-
ስለ ወይን እርሻ የተነገሩ ሁለት ምሳሌዎችኢየሱስ—መንገድ፣ እውነት፣ ሕይወት
-
-
ይሁንና “ገበሬዎቹ” ወደ እነሱ ከተላኩት “ባሪያዎች” አንዳንዶቹን አሠቃዩአቸው፤ ሌሎቹንም ገደሏቸው። ኢየሱስ እንዲህ አለ፦ “[የወይን እርሻው ባለቤት] የቀረው የሚወደው ልጁ ነበር። ‘መቼም ልጄን ያከብሩታል’ በማለት በመጨረሻ እሱን ላከው። እነዚያ ገበሬዎች ግን እርስ በርሳቸው ‘ወራሹ ይሄ ነው። ኑ እንግደለው፤ ርስቱም የእኛ ይሆናል’ ተባባሉ። ስለዚህ ይዘው ገደሉት።”—ማርቆስ 12:6-8
-
-
ስለ ወይን እርሻ የተነገሩ ሁለት ምሳሌዎችኢየሱስ—መንገድ፣ እውነት፣ ሕይወት
-
-
“በዚህ ጊዜ ጸሐፍትና የካህናት አለቆች ይህን ምሳሌ የተናገረው እነሱን አስቦ እንደሆነ” ተረዱ። (ሉቃስ 20:19) ስለዚህ ሕጋዊ ‘ወራሽ’ የሆነውን ኢየሱስን ለመግደል ከመቼውም ጊዜ ይበልጥ ቆርጠው ተነሱ። ይሁንና ሕዝቡ እንደ ነቢይ ስለሚያየው ሕዝቡን ፈሩ፤ በመሆኑም በዚህ ወቅት ሊገድሉት አልሞከሩም።
-