-
አንተ ራስህ ሲፈጸም ያየኸው የመጽሐፍ ቅዱስ ትንቢትመጽሐፍ ቅዱስ—የአምላክ ቃል ነው ወይስ የሰው?
-
-
“የምጥ ጣር መጀመሪያ”
11, 12. አንደኛው የዓለም ጦርነት “የምጥ ጣር መጀመሪያ” ብቻ ነው ሊባል የሚችለው እንዴት ነው?
11 የኢየሱስ ትንቢት የመጀመሪያዎቹ ቁጥሮች የሚደመደሙት “እነዚህም ሁሉ የምጥ ጣር መጀመሪያ ናቸው” በሚሉት ቃላት ነው። ይህ በተለይ በአንደኛው የዓለም ጦርነት ወቅት እውነት ሆኖ ታይቷል። የአንደኛው ዓለም ጦርነት በ1918 ማብቃቱ ያስገኘው ሰላም ላፍታም አልቆየም። ወዲያው በኢትዮጵያ፣ በሊቢያ፣ በስፔይን፣ በሩስያ፣ በሕንድና በሌሎችም አገሮች ላይ መለስተኛ መጠን የነበራቸው ነገር ግን አስከፊ ውጤት ያስከተሉ ወታደራዊ እርምጃዎች ተወስደዋል። ከዚያ በኋላ ደግሞ 50 ሚልዮን የሚያክሉ ወታደሮችንና ሰላማዊ ዜጎችን ሕይወት የቀጠፈውና እጅግ አስፈሪ የነበረው ሁለተኛው የዓለም ጦርነት ፈንድቷል።
12 ከዚህም በላይ ጊዜያዊ የሰላም ስምምነቶች ቢደረጉና ጦርነቶች አንዳንዴ ጋብ ቢሉም ዛሬም የሰው ልጅ ከጦርነት አላረፈም። በ1987 ሪፖርት እንደተደረገው ከ1960 ወዲህ የተደረጉት 81 ትላልቅ ጦርነቶች የ12,555,000 ወንዶች፣ ሴቶችና ሕፃናት ሕይወት እንዲቀጠፍ ምክንያት ሆነዋል። በ1987 የተካሄዱት ጦርነቶች መጠን ከዚያ ቀደም በነበረ በየትኛውም ዓመት ከተደረጉት ጦርነቶች ቁጥር እጅግ የሚበልጥ ነበር።1 ከዚህም በላይ ለጦር ዝግጅቶችና ወታደራዊ ወጪዎች በየዓመቱ የሚወጣው ጠቅላላ ገንዘብ ወደ 1,000,000,000,000 የአሜሪካ ዶላር የደረሰ ሲሆን ይህም የዓለምን ኤኮኖሚ የሚያዛባ ነው።2 ኢየሱስ ‘ሕዝብ በሕዝብ ላይ መንግሥትም በመንግሥት ላይ ይነሣል’ ሲል የተናገረው ትንቢት ፍጻሜውን እያገኘ ለመሆኑ ምንም አያጠራጥርም። ዳማው የጦርነት ፈረስ በምድር ላይ አስፈሪ ግልቢያውን ቀጥሏል። ይሁን እንጂ ስለ ምልክቱ ሁለተኛ ዘርፍ ምን ማለት ይቻላል?
-
-
አንተ ራስህ ሲፈጸም ያየኸው የመጽሐፍ ቅዱስ ትንቢትመጽሐፍ ቅዱስ—የአምላክ ቃል ነው ወይስ የሰው?
-
-
14. የኢየሱስ ትንቢት ፍጻሜውን እንዲያገኝ ያደረጉት ከ1914 ወዲህ የተከሰቱት የትኞቹ ታላላቅ ረሃቦች ናቸው?
14 አንዳንድ አገሮች ከፍተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ በደረሱበት በዛሬው ጊዜ ይህ ትንቢት ፍጻሜውን እያገኘ ነው ለማለት ይቻላልን? የመላውን ዓለም ሁኔታ መለስ ብሎ መቃኘት ለዚህ ጥያቄ የማያሻማ መልስ ይሰጠናል። ከታሪክ መረዳት እንደምንችለው የረሃብ መንስኤዎች ጦርነትና የተፈጥሮ አደጋዎች ናቸው። እንግዲያው ከአቅሙ በላይ የተፈጥሮ አደጋዎችንና ጦርነቶችን እያስተናገደ ያለው ይህ የእኛ መቶ ዘመን በተደጋጋሚ በረሃብ አለንጋ መገረፉ ምንም አያስገርምም። ከ1914 ወዲህ ብዙዎቹ የዓለም ክፍሎች በእነዚህ አደጋዎች ተጠቅተዋል። አንድ ሪፖርት እንደዘገበው ከ1914 ወዲህ ተራርቀው በሚገኙ በግሪክ፣ በኔዘርላንድስ፣ በቀድሞዋ ሶቪየት ሕብረት፣ በናይጄርያ፣ በቻድ፣ በቺሊ፣ በፔሩ፣ በባንግላዴሽ፣ በቤንጋል፣ በካምፖዲያ፣ በኢትዮጵያና በጃፓን 60 ከባድ ረሃቦች እንደደረሱ ተመዝግቧል።3 ከእነዚህ ረሃቦች መካከል አንዳንዶቹ በርከት ላሉ ዓመታት የዘለቁ ሲሆን በሚልዮን የሚቆጠሩ ሰዎችን ሕይወትም ቀጥፈዋል።
-
-
አንተ ራስህ ሲፈጸም ያየኸው የመጽሐፍ ቅዱስ ትንቢትመጽሐፍ ቅዱስ—የአምላክ ቃል ነው ወይስ የሰው?
-
-
የመሬት መንቀጥቀጦች
17. ከ1914 በኋላ ብዙም ሳይቆይ የተከሰተው ከፍተኛ ውድመት ያስከተለ የመሬት መንቀጥቀጥ የትኛው ነው?
17 አንደኛው የዓለም ጦርነት ከተጀመረ ከጥቂት ወራት በኋላ በጥር 13, 1915 በኢጣሊያ አብሩዚ ከተማ የደረሰው የመሬት መንቀጥቀጥ የ32,610 ሰዎች ሕይወት እንዲጠፋ ምክንያት ሆኗል። ይህ ከፍተኛ አደጋ በኢየሱስ መገኘት ጊዜ ከሚታዩት ጦርነቶችና ረሃብ በተጨማሪ የሚታየውን ሌላ ክስተት ያስታውሰናል:- “የምድርም መናወጥ በልዩ ልዩ ስፍራ ይሆናል።” እንደ ጦርነቱና ረሃቡ ሁሉ በአብሩዚ የደረሰው የመሬት መንቀጥቀጥም ‘የምጥ ጣር መጀመሪያ’ ብቻ ነበር።a
-
-
አንተ ራስህ ሲፈጸም ያየኸው የመጽሐፍ ቅዱስ ትንቢትመጽሐፍ ቅዱስ—የአምላክ ቃል ነው ወይስ የሰው?
-
-
20. ኢየሱስ ስለ ቸነፈር የተናገረው ትንቢት በከፊል ፍጻሜውን እንዲያገኝ ያስቻለው የትኛው ጎላ ብሎ የሚጠቀስ ወረርሽኝ ነው?
20 በ1918 እና 1919 ቁጥራቸው ከ1,000,000,000 በላይ ሰዎች በኅዳር በሽታ ተይዘው ከ20,000,000 የሚበልጡት ሞተዋል። በሽታው የገደላቸው ሰዎች ቁጥር በታላቁ ጦርነት ከሞቱት ሰዎች በልጦ ተገኝቷል።7 ከዚህም ሌላ ዛሬ የሕክምናው መስክ እጅግ አስገራሚ መሻሻሎችን ያደረገ ቢሆንም ‘ቀሳፊ በሽታዎች’ ወይም ‘ቸነፈሮች’ ይህን ትውልድ ማሰቃየታቸውን አላቆሙም። ይህ የሆነው ለምንድን ነው? አንደኛው ምክንያት ድሃ አገሮች ከሳይንሳዊ እድገት ተጠቃሚ የመሆን አጋጣሚያቸው ውስን መሆኑ ነው። ድሃ የሆኑ ሰዎች በቀላሉ ታክመው ሊድኑ ሲችሉ የገንዘብ አቅማቸው ስለማይፈቅድ ብቻ ታመው ይሞታሉ።
-
-
አንተ ራስህ ሲፈጸም ያየኸው የመጽሐፍ ቅዱስ ትንቢትመጽሐፍ ቅዱስ—የአምላክ ቃል ነው ወይስ የሰው?
-
-
a ከ1914 እስከ 1918 ባለው ጊዜ ውስጥ በአብሩዚ ከደረሰው የመሬት መንቀጥቀጥ የሚበልጡና በሬክተር መለኪያ 8 ወይም ከዚያ በላይ የደረሱ ቢያንስ አምስት የመሬት መንቀጥቀጦች ተከስተዋል። ይሁን እንጂ እነዚህ ርዕደ መሬቶች የተሰሙት ርቀው በሚገኙ የምድር ክፍሎች በመሆኑ እንደ ኢጣሊያው የመሬት መንቀጥቀጥ እምብዛም ትኩረት አልተሰጣቸውም።5
-