-
በመጽሐፍ ቅዱስ ትንቢቶች ላይ እምነት ማሳደር ሕይወትን ያድናልመጠበቂያ ግንብ—2007 | ሚያዝያ 1
-
-
በሶርያ የነበረው ሮማዊ አገረ ገዢ ሴስቲየስ ጋለስ፣ በሦስት ወራት ውስጥ 30,000 ወታደሮችን አስከትሎ የአይሁዳውያንን ዓመጽ ለመግታት ወደ ደቡብ ዘመተ። ሠራዊቱ ኢየሩሳሌም የደረሰው በዳስ በዓል ወቅት ሲሆን ብዙም ሳይቆይ ወታደሮቹ በከተማዋ ዙሪያ ያለውን አካባቢ ዘልቀው ወደ ኢየሩሳሌም ገቡ። በቁጥር ጥቂት የሆኑት ዓማጺያን ሸሽተው በቤተ መቅደሱ ግቢ ውስጥ ተሸሸጉ። የሮም ወታደሮች በቤተ መቅደሱ ዙሪያ የሚገኘውን ግንብ ማፍረስ ጀመሩ። አረማዊ ወታደሮች የይሁዳን ቅዱስ ቦታ ማርከሳቸው ለአይሁዳውያኑ በጣም አስደንጋጭ ነገር ነው! በከተማዋ ውስጥ ያሉት ክርስቲያኖች ግን ኢየሱስ የሰጣቸውን ማስጠንቀቂያ አስታወሱ። ‘የጥፋት ርኩሰት በተቀደሰው ስፍራ ቆሞ ስታዩ፣ በዚያን ጊዜ በይሁዳ የምትገኙ ወደ ተራራዎች ሽሹ’ ብሏቸው ነበር። (ማቴዎስ 24:15, 16) ኢየሱስ የተናገረውን ትንቢት አምነው እርምጃ ይወስዱ ይሆን? ከዚያ በኋላ ከተከናወኑት ሁኔታዎች መመልከት እንደሚቻለው በሕይወት መትረፋቸው የተመካው የኢየሱስን ማስጠንቀቂያ በመስማታቸው ላይ ነው። ይሁን እንጂ እንዴት መሸሽ ይችላሉ?
ሴስትየስ ጋለስ በድንገትና ባልታወቀ ምክንያት ሠራዊቱን ይዞ ወደ ባሕሩ ዳርቻ አፈገፈገ፤ ዓማጺያኑም ሮማውያኑን እየተከታተሉ አሳደዷቸው። በዚህ መንገድ በከተማዋ ላይ አንዣብቦ የነበረው መከራ በአስገራሚ ሁኔታ በአጭሩ ተገታ! ክርስቲያኖችም ኢየሱስ በተናገረው ትንቢታዊ ማስጠንቀቂያ ላይ እምነት በማሳደር ከኢየሩሳሌም ወጥተው ከዮርዳኖስ ወንዝ ባሻገር በተራራው ላይ ወደምትገኝ ፔላ የተባለች ገለልተኛ ከተማ ሸሹ። እነዚህ ክርስቲያኖች በጥሩ ጊዜ አምልጠዋል። ብዙም ሳይቆይ ዓማጺያኑ ወደ ኢየሩሳሌም የተመለሱ ሲሆን የቀሩትን የከተማዋ ነዋሪዎች በዓመጹ እንዲተባበሯቸው ማስገደድ ጀመሩ።a አስተማማኝ መሸሸጊያ ያገኙት በፔላ ያሉት ክርስቲያኖች ግን እዚያው ሆነው ሁኔታውን እየተከታተሉ ነው።
-
-
በመጽሐፍ ቅዱስ ትንቢቶች ላይ እምነት ማሳደር ሕይወትን ያድናልመጠበቂያ ግንብ—2007 | ሚያዝያ 1
-
-
a የአይሁድ ታሪክ ጸሐፊ የሆነው ጆሴፈስ እንደዘገበው ዓማጺያኑ ወደ ኢየሩሳሌም ከመመለሳቸው በፊት ሮማውያንን ለሰባት ቀናት አሳድደዋቸዋል።
-