-
እውነተኛ ደስታ ማግኘት የሚቻለው ከየት ነው?መጠበቂያ ግንብ—1997 | መጋቢት 15
-
-
ኢየሱስ ክርስቶስ በተራራ ስብከቱ ላይ እንዲህ ብሏል:- “በመንፈሳዊ የጎደላቸው ነገር እንዳለ የሚታወቃቸው ደስተኞች ናቸው። መንግሥተ ሰማያት የእነሱ ነውና።” (ማቴዎስ 5:3 NW ) በተጨማሪም ኢየሱስ “የሰው ሕይወት በገንዘቡ ብዛት አይደለምና፤ ተጠንቀቁ፤ ከመጎምጀትም ሁሉ ተጠበቁ” ብሏል።— ሉቃስ 12:15
-
-
እውነተኛ ደስታ ማግኘት የሚቻለው ከየት ነው?መጠበቂያ ግንብ—1997 | መጋቢት 15
-
-
ሌሎች ደግሞ ለራሳቸው ያላቸውን ግምት ከፍ ለማድረግ በመጣር ደስታ ለማግኘት በሚያደርጉት ፍለጋ በውስጣዊ ማንነታቸው ላይ አተኩረዋል። ቤተ መጻሕፍትና የመጻሕፍት መሸጫ መደብሮች ራስን በራስ ማስተማር በሚቻልባቸው መጻሕፍት የተሞሉ ቢሆንም እነዚህ ጽሑፎች ለሰዎች ዘላቂ ደስታ አላመጡላቸውም። ታዲያ እውነተኛ ደስታ ማግኘት የምንችለው ከየት ነው?
እውነተኛ ደስታ ለማግኘት ከፈለግን በተፈጥሯችን ለመንፈሳዊ ነገሮች ያለንን ፍላጎት መገንዘብ አለብን። ኢየሱስ “በመንፈሳዊ የጎደላቸው ነገር እንዳለ የሚታወቃቸው ደስተኞች ናቸው” ብሏል። እርግጥ ይህን ፍላጎታችንን ተረድተን ምንም ሳናደርግ ብንቀር የምናገኘው ጥቅም አይኖርም። ጉዳዩን በምሳሌ ለማስረዳት ያህል:- አንድ የማራቶን ሯጭ ከውድድሩ በኋላ የውኃ ጥማቱን ሳያረካ ቢቀር ምን ይደርስበታል? ወዲያውኑ በሰውነቱ ውስጥ ያለው ፈሳሽ አልቆ ሌሎች ከባድ ችግሮች አያጋጥሙትም? በተመሳሳይም የመንፈሳዊ ምግብ ፍላጎታችንን ሳናሟላ ብንቀር የኋላ ኋላ በመንፈሳዊ እንዳከማለን። ይህ ደግሞ ደስታ ማጣት ያስከትላል።
-