-
በክርስቶስ መገኘት ላይ ብርሃን እንዲፈነጥቅ ማድረግመጠበቂያ ግንብ—1993 | ግንቦት 1
-
-
8, 9. (ሀ) የኢየሱስ ንጉሣዊ መገኘት ምንን ያጠቃልላል? (ለ) ኢየሱስ ሐሰተኛ ክርስቶሶችን በሚመለከት የሰጠው ትንቢት እርሱ ስለሚገኝበት ቦታና ሁኔታ ምን ያመለክታል?
8 የኢየሱስ ንግሥና መላዋን ምድር የሚያጠቃልል ስለሆነ እውነተኛ አምልኮ በሁሉም አህጉራት እየተስፋፋ ነው። ንጉሣዊ መገኘቱ (ፓሩሲያ) ምድር አቀፍ ምርመራ የሚካሄድበት ጊዜ ነው። (1 ጴጥሮስ 2:12) ይሁን እንጂ ኢየሱስን አግኝቶ ምክር መጠየቅ የሚቻልበት ዋና ከተማ ወይም ማዕከል ይኖራልን? ኢየሱስ ለዚህ ጥያቄ መልስ ሲሰጥ የእርሱ መገኘት በሚጠበቅበት ጊዜ ሐሰተኛ ክርስቶሶች እንደሚነሱ ተንብዮአል። እንዲህ ሲልም አስጠነቀቀ፦ “እንግዲህ እነሆ፣ [ክርስቶስ] በበረሀ ነው ቢሉአችሁ፣ አትውጡ፤ እነሆ፣ በእልፍኝ ነው ቢሉአችሁ፣ አትመኑ፤ መብረቅ ከምሥራቅ ወጥቶ እስከ ምዕራብ እንደሚታይ፣ የሰው ልጅ መገኘት [ፓሩሲያ] እንዲሁ ይሆናልና።”—ማቴዎስ 24:24, 26, 27 አዓት
-
-
በክርስቶስ መገኘት ላይ ብርሃን እንዲፈነጥቅ ማድረግመጠበቂያ ግንብ—1993 | ግንቦት 1
-
-
10. የመጽሐፍ ቅዱስ እውነት መብረቆች በመላው ምድር ላይ ብርሃናቸው የታየው እንዴት ነው?
10 እንዲያውም ኢየሱስ ንጉሥ ሆኖ መምጣቱን ወይም ንጉሣዊ መገኘቱን ስለ መጀመሩ የሚደበቅ ምንም ነገር አይኖርም። ኢየሱስ አስቀድሞ እንደተነበየው የመጽሐፍ ቅዱስ እውነቶች እንደ መብረቅ በመላው ምድር ላይ ከምዕራብ እስከ ምሥራቅ ማብራታቸውን ቀጥለዋል። በእርግጥም የይሖዋ ምስክሮች ዘመናዊ ብርሃን አብሪዎች በመሆን ‘እስከ ምድር ዳር ድረስ [የይሖዋ] መድኃኒት ይመጣ ዘንድ ለአሕዛብ ብርሃን ሆነዋል።—ኢሳይያስ 49:6
-