የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • የበጎቹና የፍየሎቹ የወደፊት ዕጣ ምንድን ነው?
    መጠበቂያ ግንብ—1995 | ጥቅምት 15
    • 4. በበጎቹና በፍየሎቹ ምሳሌ መጀመሪያ ላይ ስለ ኢየሱስ የተጠቀሰው ምንድን ነው? ሌሎችስ እነማን ተጠቅሰዋል?

      4 ኢየሱስ ምሳሌውን የጀመረው ‘የሰው ልጅ በሚመጣበት ጊዜ’ በማለት ነው። “የሰው ልጅ” ማን እንደሆነ ሳታውቅ አትቀርም። የወንጌል ጸሐፊዎች ብዙውን ጊዜ የሰው ልጅ የሚለውን አጠራር ኢየሱስን ለመግለጽ ይጠቀሙበታል። ኢየሱስ ራሱ እንኳ ራሱን የሰው ልጅ ብሎ የጠራው “የሰው ልጅ የሚመስል” “ግዛትና ክብር መንግሥትም” ለመቀበል በዘመናት ወደ ሸመገለው እንደ ቀረበ የሚገልጸውን የዳንኤል ራእይ በአእምሮው ይዞ እንደ ነበረ አያጠራጥርም። (ዳንኤል 7:13, 14፤ ማቴዎስ 26:63, 64፤ ማርቆስ 14:61, 62) በዚህ ምሳሌ ውስጥ በዋነኛነት የተጠቀሰው ኢየሱስ ቢሆንም ሌሎችም አሉ። በማቴዎስ 24:30, 31 ላይ እንደ ተገለጸው ቀደም ሲል በዚህ ንግግሩ ውስጥ የሰው ልጅ ‘በኃይልና በብዙ ክብር ሲመጣ’ መላእክት ከፍተኛ ሚና እንደሚጫወቱ ተናግሮ ነበር። በተመሳሳይም የበጎቹና የፍየሎቹ ምሳሌ ኢየሱስ ‘በክብሩ ዙፋን ላይ’ ለፍርድ ‘ሲቀመጥ’ መላእክት ከእሱ ጋር እንደሚኖሩ ያሳያል። (ከማቴዎስ 16:27 ጋር አወዳድር።) ይሁን እንጂ ዳኛውና መላእክቱ በሰማይ ስለሆኑ በምሳሌው ውስጥ የተጠቀሱት ሰዎች በሰማይ ናቸውን?

  • የበጎቹና የፍየሎቹ የወደፊት ዕጣ ምንድን ነው?
    መጠበቂያ ግንብ—1995 | ጥቅምት 15
    • መላእክቱንም ይልካቸዋል ከመላእክት ጋር ይመጣል

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ