-
አምላክን እንድታገለግሉ የሚገፋፋችሁ ምንድን ነው?መጠበቂያ ግንብ—1995 | ሰኔ 15
-
-
17. የመክሊቶቹን ምሳሌ በራስህ አባባል በአጭሩ ግለጽ።
17 በማቴዎስ 25:14–30 ላይ የተመዘገበውን ስለ መክሊቶቹ የሚናገረውን የኢየሱስ ምሳሌ ተመልከት። አንድ ወደ ሩቅ አገር የሚሄድ ሰው ባሪያዎቹን ጠርቶ ንብረቱን አከፋፈላቸው። “ለእያንዳንዱ እንደ ዓቅሙ፣ ለአንዱ አምስት መክሊት ለአንዱ ሁለት ለአንዱም አንድ ሰጠ።” ጌታው ሒሳቡን ከባሪያዎቹ ጋር ለመተሳሰብ ሲመጣ ምን አገኘ? አምስት መክሊቶች የተሰጠው ባሪያ ሌሎች አምስት መክሊቶችን አተረፈ። በተመሳሳይም ሁለት መክሊቶች የተሰጠው ባሪያ ሌሎች ሁለት መክሊቶችን አተረፈ። አንድ መክሊት የተሰጠው ባሪያ መክሊቱን ቀበረው፤ የጌታውን ሀብት ከፍ ለማድረግ ምንም ያደረገው ነገር አልነበረም። ጌታው ሁኔታውን የተመለከተው እንዴት ነው?
18, 19. (ሀ) ጌታው ሁለት መክሊቶች የሰጠውን ባሪያ አምስት መክሊቶችን ከሰጠው ባሪያ ጋር ያላወዳደረው ለምንድን ነው? (ለ) የመክሊቶቹ ምሳሌ ስለ ማመስገንና ራሳችንን ከሌሎች ጋር ስለ ማወዳደር ምን ያስተምረናል? (ሐ) ሦስተኛው ባሪያ የተፈረደበት ለምንድን ነው?
18 በመጀመሪያ ደረጃ አምስት መክሊቶችና ሁለት መክሊቶች ተሰጥቷቸው የነበሩትን ባሪያዎች በየተራ እንመልከት። ሁለቱንም ባሪያዎች ጌታቸው “አንተ በጎ ታማኝም ባሪያ!” ብሏቸዋል። አምስት መክሊቶች የተሰጠው ባሪያ ሁለት መክሊቶች ብቻ ቢያተርፍ ኖሮ ይህን ይለው ነበር? ሊለው አይችልም! በሌላ በኩል ደግሞ ሁለት መክሊቶችን ያተረፈውን ባሪያ ‘አምስት መክሊቶችን ለምን አላተረፍክም? ይህ ባሪያ ምን ያህል እንዳተረፈልኝ ትመለከታለህ!’ አላለውም። አዎን፣ በኢየሱስ የተመሰለው ርኁሩኁ ጌታ ሰዎችን ከሰዎች ጋር አያወዳድርም። መክሊቶች የሰጣቸው “እንደ ዓቅማቸው” ስለሆነ እያንዳንዳቸው ከሚችሉት በላይ እንዲመልሱ አልጠበቀባቸውም። ሁለቱም ለጌታቸው በሙሉ ነፍሳቸው ስለሠሩ እኩል ተመስግነዋል። ሁላችንም ከዚህ ትምህርት ማግኘት እንቸላለን።
-
-
አምላክን እንድታገለግሉ የሚገፋፋችሁ ምንድን ነው?መጠበቂያ ግንብ—1995 | ሰኔ 15
-
-
20. ይሖዋ አቅማችንን የሚመለከተው እንዴት ነው?
20 ይሖዋ ሁላችንም በፍጹም ኃይላችን እንድንወደው ቢጠብቅብንም ‘እርሱ ራሱ ፍጥረታችንን የሚያውቅና እኛ አፈር መሆናችንን የሚያስብ’ መሆኑን ማወቅ ምንኛ የሚያስደስት ነው! (መዝሙር 103:14) ምሳሌ 21:2 ይሖዋ የአገልግሎት አሃዞችን ሳይሆን “ልብን ይመዝናል” ይላል። ከአቅማችን በላይ የሆኑ የገንዘብ፣ የአካል፣ የስሜት ወይም ሌሎች ችግሮቻችንን ይረዳልናል። (ኢሳይያስ 63:9) ሆኖም ያሉንን ጥሪቶች በሙሉ የምንችለውን ያህል እንድንጠቀምባቸው ይጠብቅብናል። ይሖዋ ፍጹም ቢሆንም ፍጹማን ካልሆኑ አምላኪዎቹ ጋር ባለው ግንኙነት ከእነሱ ፍጽምናን አይጠብቅባቸውም። ይሖዋ ከሰዎች ጋር ባለው ግንኙነት ሁሉ ምክንያታዊ ነው፤ ከአቅም በላይ የሆኑ ነገሮችን አይጠብቅም።
-