-
“የሰላሙ መስፍን” “ደስታ” ተካፋይ መሆን“የሰላሙ መስፍን“ ሲገዛ በምድር ዙሪያ የሚገኝ ዋስትና ያለው ሕይወት
-
-
2. (ሀ) ኢየሱስን በሚመለከት የሃብታሙ ሰው ወደ ሌላ አገር መጓዝ ምንን ያመለከታል? እርሱስ የሄደው ወደ ማን ነበር? (ለ) ጌታው ይዞ የተመለሰው ምንድን ነው?
2 በምሳሌው ውስጥ የተጠቀሰው ሀብታም ሰው ኢየሱስ ክርስቶስን ስለሚያመለክት ሰውየው ረጅም ጉዞ ለማድረግ ወደ ሌላ አገር መሄዱ ኢየሱስ ከፊቱ የሚጠብቀውን ደስታ ወደሚሰጠው አምላክ መሄዱን ያመለክታል። ታዲያ እርሱ የሄደው ወደ ማን ነበር? ዕብራውያን 12:2 ይነግረናል:- “የእምነታችንንም ራስና ፈጻሚውን ኢየሱስን ተመልክተን፣ በፊታችን ያለውን ሩጫ በትዕግሥት እንሩጥ፤ እርሱ ነውርን ንቆ በፊቱም ስላለው ደስታ በመስቀል ታግሶ በእግዚአብሔር ዙፋን ቀኝ ተቀምጧልና።” አዎን በእርግጥም የዚያ ደስታ ምንጭ ይሖዋ አምላክ ነው። ኢየሱስ በምድር ላይ ላሉት ታማኝ ደቀመዛሙርቱ “መክሊት” በአደራ በመስጠት ትቷቸው የሄደው ወደ እርሱ ነበር። ጌታው ለሦስቱ ባሮች ስምንት መክሊቶችን በሰጠበት ጊዜ ያልነበሩትን ሌሎች “ብዙ ነገሮች” ይዞ ተመለሰ። ቀደም ብሎ ኢየሱስ የሰጠው ምሳሌ ማለትም ‘የአሥሩ ምናን’ ምሳሌ እርሱ ይዞ የተመለሰው ‘ንጉሣዊ ሥልጣንን’ እንደሆነ ይገልጻል።— ሉቃስ 19:12–15 አዓት
-
-
“የሰላሙ መስፍን” “ደስታ” ተካፋይ መሆን“የሰላሙ መስፍን“ ሲገዛ በምድር ዙሪያ የሚገኝ ዋስትና ያለው ሕይወት
-
-
4. ንጉሥ ሆኖ ከተሾመ በኋላ ኢየሱስ ክርስቶስ ታማኝ “ባሮቹን” ወደ አስደሳች ሁኔታ ለመጋበዝ ልዩ ምክንያት የነበረው ለምንድን ነው?
4 እርሱ ለኢየሩሳሌም ነዋሪዎች ራሱን በይሖዋ መንፈስ ለንጉሥነት እንደተቀባ ብቻ አድርጎ ያቀረበበት ወቅት የደስታ ጊዜ ከነበረ በአሕዛብ ዘመን ፍጻሜ በ1914 ንጉሥ ሆኖ ሲሾም ምን ያህል የበለጠ ደስታ ሆኖ ነበር? ይህ ለእርሱ በጣም አስደሳች ጊዜ ነበር። በእርግጥም በዚያን ጊዜ ከዚያ በፊት በፍጹም ታይቶ ወደማይታወቅ ደስታ ገብቶ ነበር። ስለዚህ ሂሳቡን ከእነርሱ ጋር በሚተሳሰብበት ጊዜ ‘በጎና ታማኝ’ ብሎ ለጠራቸው ደቀመዛሙርቱ:- “በጥቂቱ ታምነሃል፣ በብዙ እሾምሃለሁ ወደ ጌታህ ደስታ ግባ” ሊላቸው ችሎ ነበር። (ማቴዎስ 25:21) ተቀባይነት ያገኙት “ባሪያዎቹ” አሁን ሊካፈሉ የሚችሉበት አዲስ ደስታ መጥቶ ነበር። እንዴት ያለ ሽልማት ነው!
5. (ሀ) ሐዋርያው ጳውሎስ የክርስቶስ “አምባሳደር” ሲሆን ሁኔታዎቹ እንዴት ያሉ ነበሩ? (ለ) ይሁን እንጂ ዛሬ ቅቡዓን ቀሪዎች የክርስቶስ “አምባሳደሮች” የሆኑት ምን አዲስ ሁኔታዎች ከተፈጠሩ በኋላ ነው?
5 በመግዛት ላይ ያለው ንጉሥ የኢየሱስ ክርስቶስ ቅቡዓን ደቀ መዛሙርት በ1919 ተቀባይነት ወደሚያገኙበት ሁኔታ ገብተው ነበር፤ ይህም ከፍተኛ ደስታ አመጣላቸው። ከአሥራ ዘጠኝ መቶ ዘመናት በፊት ሐዋርያው ጳውሎስ የእምነት ጓደኞቹ ስላላቸው ከፍተኛ ቦታ ሲነግራቸው “ስለ ክርስቶስ መልዕክተኞች [አምባሳደሮች] ነን” ብሎ ጽፎላቸው ነበር። (2 ቆሮንቶስ 5:20) ይህ የተጻፈው ኢየሱስ ገና “መንግሥተ ሰማያትን” ለመቀበል ሕጋዊ ወራሽ ብቻ ሆኖ በተስፋ በሚጠባበቅበት ጊዜ ነው። (ማቴዎስ 25:1) ስለዚህም በዚያን ጊዜ በአባቱ ቀኝ መቀመጥና የሚሾምበትን ቀን መጠበቅ ያስፈልገው ነበር። ይሁን እንጂ ሞገስ ያገኙት ቀሪዎች አሁን ከ1919 ወዲህ “አምባሰደሮች” በመሆን እየገዛ ባለው ንጉሥ ተልከዋል። (ዕብራውያን 10:12, 13) ይህ እውነታ በ1922 በሴዳር ፖይንት ኦሃዮ በተደረገው ስብሰባ ላይ ለዓለም አቀፍ የመጽሐፍ ቅዱስ ተማሪዎች ተገልጾላቸው ነበር።
-