የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • ከታላንቱ ምሳሌ ትምህርት ማግኘት
    መጠበቂያ ግንብ—2015 | መጋቢት 15
    • ክፉና ሰነፍ ባሪያ

      14, 15. ኢየሱስ ከቅቡዓን ወንድሞቹ መካከል ብዙዎች ክፉና ሰነፍ እንደሚሆኑ መግለጹ ነበር? አብራራ።

      14 በምሳሌው ላይ የተጠቀሰው የመጨረሻው ባሪያ በታላንቱ ከመነገድ፣ ሌላው ቀርቶ ታላንቱን ገንዘብ ለዋጮች ጋር ከማስቀመጥ ይልቅ መሬት ውስጥ ቀብሮታል። ይህ ባሪያ የጌታውን ጥቅም የሚነካ ነገር ሆን ብሎ በማድረጉ መጥፎ ዝንባሌ እንዳለው አሳይቷል። ጌታው “ክፉና ሰነፍ” ብሎ የጠራው መሆኑ የሚያስገርም አይደለም። ጌታው፣ የእሱን ታላንት ወስዶ አሥር ታላንት ላለው ባሪያ ሰጠው። ከዚያም ጌታው ክፉውን ባሪያ አስመልክቶ እንዲህ አለ፦ “ውጭ ወዳለው ጨለማ ጣሉት። በዚያም ያለቅሳል፣ በሐዘንም ጥርሱን ያፋጫል።”—ማቴ. 25:24-30፤ ሉቃስ 19:22, 23

      15 ኢየሱስ ከጌታው ሦስት ባሪያዎች አንዱ ታላንቱን እንደቀበረው ሲገልጽ ከቅቡዓን ተከታዮቹ መካከል አንድ ሦስተኛ የሚሆኑት ክፉና ሰነፍ እንደሚሆኑ መጠቆሙ ነበር? በፍጹም። የምሳሌውን አውድ እንመልከት። ኢየሱስ ስለ ታማኝና ልባም ባሪያ በተናገረው ምሳሌ ላይ ባልንጀራዎቹ የሆኑትን ባሪያዎች ስለሚደበድብ ክፉ ባሪያ ጠቅሶ ነበር። ኢየሱስ ይህን ሲል ክፉ ባሪያ የሆነ ቡድን እንደሚኖር መናገሩ አልነበረም። ከዚህ ይልቅ ታማኙ ባሪያ፣ የክፉ ባሪያ ዓይነት ባሕርያት እንዳያንጸባርቅ ማሳሰቡ ነበር። በተመሳሳይም ኢየሱስ ስለ አሥሩ ደናግል በተናገረው ምሳሌ ላይ ከቅቡዓን ተከታዮቹ መካከል ግማሽ የሚሆኑት እንደ አምስቱ ሞኝ ደናግል እንደሚሆኑ መግለጹ አልነበረም። ከዚህ በተቃራኒ መንፈሳዊ ወንድሞቹ ንቁና ዝግጁ ካልሆኑ ምን ሊከሰት እንደሚችል ማስጠንቀቁ ነበር።f ከዚህ አንጻር፣ ኢየሱስ ስለ ታላንቱ የሚገልጸውን ምሳሌ ሲናገር በመጨረሻዎቹ ቀናት ከሚኖሩት ቅቡዓን ወንድሞቹ መካከል ብዙዎች ክፉና ሰነፍ እንደሚሆኑ እየገለጸ አልነበረም ብሎ መደምደሙ ምክንያታዊ ይመስላል። ከዚህ ይልቅ ቅቡዓን ተከታዮቹ ምንጊዜም በትጋት እንዲሠሩ ማለትም በታላንታቸው ‘እንዲነግዱ’ እንዲሁም ክፉው ባሪያ ካሳየው ዝንባሌና ካደረገው ነገር እንዲርቁ እያስጠነቀቃቸው ነው።—ማቴ. 25:16

  • ከታላንቱ ምሳሌ ትምህርት ማግኘት
    መጠበቂያ ግንብ—2015 | መጋቢት 15
    • ክፉውና ሰነፉ ባሪያ ማን ነው?

      ጌታው ክፉው ባሪያ ወደ ውጭ እንዲጣል ሲያዝዝ

      የቀድሞው ማብራሪያ፦ ክፉውና ሰነፉ ባሪያ የሚያመለክተው በ1914 አካባቢ የነበሩ በስብከቱ ሥራ ለመካፈል ፈቃደኛ ያልሆኑ ቅቡዓንን ነው።

      የተስተካከለው ማብራሪያ፦ ኢየሱስ ከቅቡዓን ተከታዮቹ መካከል የተወሰኑት ክፉ ባሪያ እንደሚሆኑ አስቀድሞ መናገሩ አልነበረም። ከዚህ ይልቅ ክርስቶስ፣ ተከታዮቹን ክፉና ሰነፍ እንደሆኑ አድርጎ እንዲመለከታቸው የሚያደርግ አስተሳሰብ ወይም ድርጊት ቢኖራቸው ምን እንደሚያጋጥማቸው ማስጠንቀቁ ነበር።

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ