-
በፍርድ ዙፋኑ ፊት የምትቀርበው እንዴት ነው?መጠበቂያ ግንብ—1995 | ጥቅምት 15
-
-
21 የሰው ልጅ በክብሩ በሚመጣበት ጊዜ በእነዚህ ብሔራት ውስጥ የሚገኙ ሰዎች ምን ዋጋ ይቀበላሉ? “የሰው ልጅ በከብሩ በሚመጣበት ጊዜ ከእርሱም ጋር ቅዱሳን መላእክቱ ሁሉ፣ በዚያን ጊዜ በክብሩ ዙፋን ይቀመጣል” በማለት ከሚጀምረው ስለ በጎችና ፍየሎች ከሚናገረው ምሳሌ መልሱን ለማግኘት እንሞክር።—ማቴዎስ 25:31, 32
22, 23. የበጎቹና የፍየሎቹ ምሳሌ በ1914 መፈጸም አለመጀመሩን የሚያመለክቱት የትኞቹ ነጥቦች ናቸው?
22 ኢየሱስ በ1914 በንጉሣዊ ሥልጣኑ ላይ እንደ ተቀመጠ ከብዙ ጊዜ በፊት ተረድተን ነበር፤ ታዲያ ይህ ምሳሌ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ በመፈጸም ላይ ነውን? ማቴዎስ 25:34 ኢየሱስን እንደ ንጉሥ አድርጎ ስለሚገልጸው ይህ ምሳሌ ከ1914 ጀምሮ መፈጸም ጀምሯል ብሎ ማሰብ ምክንያታዊ ነው። ይሁን እንጂ ከዚያ ጊዜ በኋላ ወዲያውኑ የተሰጠው ፍርድ ምን ነበር? “በአሕዛብ ሁሉ” ላይ ፍርድ አልተሰጠም። ከዚህ ይልቅ ‘የእግዚአብሔር ቤት’ ነን በሚሉት ላይ ትኩረቱን አድርጓል። (1 ጴጥሮስ 4:17) ከሚልክያስ 3:1–3 ጋር በሚስማማ መንገድ ኢየሱስ እንደ የይሖዋ መልእክተኛ በመሆን በምድር ላይ በቀሩት ቅቡዓን ክርስቲያኖች ላይ ፍርድ በመስጠት ምርመራ አካሂዷል። በተጨማሪም በሐሰት “የእግዚአብሔር ቤት” ነኝ በምትለዋ በሕዝበ ክርስትና ላይ ፍርድ የሚሰጥበት ጊዜ ነበር።c (ራእይ 17:1, 2፤ 18:4–8) ይሁን እንጂ በዚያን ጊዜ ወይም ከዚያ ጊዜ ጀምሮ ኢየሱስ አሕዛብን ሁሉ በጎችና ፍየሎች ናችሁ በማለት የመጨረሻ ፍርድ ለመስጠት እንደተቀመጠ የሚያሳይ ምንም ማስረጃ የለም።
23 ኢየሱስ በምሳሌው ውስጥ የሚያከናውነውን ተግባር ከመረመርን በመጨረሻ በአሕዛብ ሁሉ ላይ ሲፈርድ እንመለከተዋለን። ምሳሌው ባለፉት አሥርተ ዓመታት የሞቱት ሰዎች ሁሉ ዘላለማዊ ሞት ወይም ሕይወት እየተፈረደባቸው ወይም እየተፈረደላቸው ይህ ፍርድ ለብዙ ዓመታት እንደሚቀጥል አያመለክትም። በቅርብ ዓመታት የሞቱ አብዛኞቹ ሰዎች ወደ ሰው ልጆች ተራ መቃብር የሄዱ ይመስላል። (ራእይ 6:8፤ 20:13) ሆኖም ምሳሌው ኢየሱስ በሕይወት የሚኖሩትንና የፍርድ ውሳኔውን የሚቀበሉትን “አሕዛብን ሁሉ” የሚዳኝበትን ጊዜ ይገልጻል።
-
-
የበጎቹና የፍየሎቹ የወደፊት ዕጣ ምንድን ነው?መጠበቂያ ግንብ—1995 | ጥቅምት 15
-
-
“እረኛም በጎቹን ከፍየሎች እንደሚለይ እርስ በርሳቸው ይለያቸዋል።” —ማቴዎስ 25:32
-
-
የበጎቹና የፍየሎቹ የወደፊት ዕጣ ምንድን ነው?መጠበቂያ ግንብ—1995 | ጥቅምት 15
-
-
3. ኢየሱስ ቀደም ሲል ባቀረበው ንግግሩ ላይ ታላቁ መከራ ከጀመረ በኋላ ወዲያውኑ ምን ይሆናል ብሎ ነበር?
3 ኢየሱስ ታላቁ መከራ ከፈነዳ “በኋላ ወዲያው” እንደሚከሰቱ የምንጠብቃቸውን አስደንጋጭ ሁኔታዎች አስቀድሞ ተናግሯል። በዚያን ጊዜ “የሰው ልጅ ምልክት” ይታያል ብሏል። ይህ ሁኔታ “የሰው ልጅ በኃይልና በብዙ ክብር በሰማይ ደመና ሲመጣ” የሚያዩትን “የምድር ወገኖች” በከፍተኛ ደረጃ ይነካል። የሰው ልጅ “ከመላእክቱ” ጋር ይመጣል። (ማቴዎስ 24:21, 29–31)a የበጎቹና የፍየሎቹ ምሳሌ የሚፈጸመው እንዴት ነው? ዘመናዊ መጽሐፍ ቅዱሶች በምዕራፍ 25 ውስጥ ያስቀምጡት እንጂ ይህ ምሳሌ ኢየሱስ ለቀረበለት ጥያቄ የሰጠው መልስ ክፍል ሲሆን በክብሩ ስለሚመጣበት ጊዜ ተጨማሪ ማብራሪያ የሚገኝበትና “በአሕዛብ ላይ” በመፍረድ ሥራው ላይ የሚያተኩር ነው።—ማቴዎስ 25:32
-