-
“አዲሲቱ ዓለም ትርጉም”—ምሁራን እውነተኛ ሆኖ አግኝተውታልመጠበቂያ ግንብ—1991 | መጋቢት 1
-
-
በአዲሲቱ ዓለም ትርጉም መሠረት ኢየሱስ የጌታን እራት በዓል ሲያቋቁም ለደቀ መዛሙርቱ ስላሳለፈው ቂጣ ማቴዎስ 26:26 እንዲህ ይላል፦ “ይህ ሥጋዬ ማለት ነው።” አብዛኞቹ ሌሎች ትርጉሞች ግን ይህን ቁጥር “ይህ ሥጋዬ ነው” በማለት ተርጉመውታል። ይህም በጌታ እራት በዓል ወቅት ቂጣው ቃል በቃል ክርስቶስ ሥጋ ይሆናል ብሎ የሚያስተምረውን መሠረተ ትምህርት ለመደገፍ እየተሠራበት ነው። በአዲሲቱ ዓለም ትርጉም ‘ማለት’ ተብሎ የተተረጐመው ቃል (ኤስቲን ኤሜይ የሚለው ቃል ዓይነት ወይም ዝርያ) የመጣው ትርጉሙ ‘መሆን’ ከሚል የግሪክ ቃል ሲሆን ‘ማለት’ የሚል ትርጉም ያመለክታል። በመሆኑም የታየር ግሪክ ሌክሲኮን ኦቭ ዘ ኒው ቴስታመንት ይህ ግሥ ምን ከማለት ጋር ተመሳሳይ እንደሆነ በመግለጽ ትርጉማቸው ‘ማመልከት’ የሆነ ሦስት የተለያዩ የእንግሊዝና ቃላትን ማለትም (to denote, signify, import) ተጠቅመዋል። በእርግጥም እዚህ ላይ ተገቢው ትርጉም ‘ማለት’ የሚለው ቃል ነው። ኢየሱስ የመጨረሻውን እራት በዓል ሲያቋቁም ሥጋው ገና በአጥንቱ ላይ ነበር። ታዲያ እንዴት አድርጐ ነው ቂጣው ቃል በቃል የእርሱ ሥጋ ሊሆን የሚችለው?a
-
-
“አዲሲቱ ዓለም ትርጉም”—ምሁራን እውነተኛ ሆኖ አግኝተውታልመጠበቂያ ግንብ—1991 | መጋቢት 1
-
-
a በራእይ 1:20 ላይ የጀርመንኛ ተርጓሚ ኩርት እስቴጅ ይህንኑ ግሥ እንደሚከተለው ተርጉሞታል፦ “ሰባቱ መቅረዞች ማለት (ኤይንሲ) ሰባቱ ጉባኤዎች ናቸው።” ፍሪዝ ቲልማንና ሉድዊግ ቲምም በተመሳሳይ በማቴዎስ 12:7 ላይ ኤስቲንን ‘ማለት’ ብለው ተርጉመውታል።
-