-
“እነሆ! ሰውዬው!”መጠበቂያ ግንብ—1991 | ጥር 1
-
-
ስለዚህ ጲላጦስ ትክክል እንደሆነ ያወቀውን ነገር ከማድረግ ይልቅ ሕዝቡን ለማስደሰት ሲል በርባንን ፈታላቸው። ኢየሱስንም ወሰደ ልብሱን አስወልቆ አስገረፈው። ይህ ተራ ግርፋት አልነበረም። የአሜሪካ ሕክምና ማህበር መጽሔት ሮማውያን ሰዎችን የሚገርፉበትን ሁኔታ ይገልጻል።
“የተለመደው መሣሪያ የተቆጣጠሩ የቆዳ ዘርፎች ያሉት አጭር አለንጋ ነበር። በቋጠሮዎቹ ላይ ትናንሽ የብረት እንክብሎች ወይም የሾሉ የበግ አጥንቶች ይታሠሩ ነበር። . . . ሮማውያን ወታደሮች የሚገረፈውን ሰው ጀርባ በሙሉ ኃይላቸው በሚመቱበት ጊዜ የብረት እንክብሎቹ ጠልቀው በመግባት በሰውነቱ ላይ ጉዳት ሲያደርሱ የተቆጣጠሩት ቆዳዎችና ሹል አጥንቶች ደግሞ ቆዳውንና በቆዳው አካባቢ ያሉትን የሰውነት ክፍሎች ይቆራርጣሉ። ግርፋቱ በቀጠለ መጠን የቆዳው ስንጥቅ እየጠለቀ ይሄድና ከሥር ያሉትን ጡንቻዎች እየቆራረጠ ወደ ውጭ ያወጣል።”
-
-
“እነሆ! ሰውዬው!”መጠበቂያ ግንብ—1991 | ጥር 1
-
-
በምድር ላይ ከኖሩት ሰዎች ሁሉ የበለጠው ሰው ተደብድቦና ቆስሎ ከፊታቸው ቆሟል! አዎ፣ ኢየሱስ ታላቅነቱን የሚያስመሰክርለት ግርማና እርጋታ ነበረው። ጲላጦስም የአክብሮትና የሐዘኔታ ስሜት የተቀላቀለበት ቃል የተናገረው ለዚህ ነበር። ዮሐንስ 18:39–19:5፤ ማቴዎስ 27:15-17, 20-30፤ ማርቆስ 15:6-19፤ ሉቃስ 23:18-25
-