የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • ከሰዎች ጋር ምን ዓይነት ግንኙነት ሊኖረን ይገባል?
    መጠበቂያ ግንብ—2008 | ግንቦት 15
    • 12. (ሀ) ኢየሱስ ስለ መንፈሳዊ ብርሃን ምን ብሏል? (ለ) ብርሃናችንን ማብራት የምንችለው እንዴት ነው?

      12 ሰዎች ከአምላክ የሚገኘውን መንፈሳዊ ብርሃን እንዲያገኙ ስንረዳቸው ከሁሉ የላቀ መልካም ነገር እያደረግንላቸው ነው። (መዝ. 43:3) ኢየሱስ፣ ደቀ መዛሙርቱ “የዓለም ብርሃን” እንደሆኑ የነገራቸው ሲሆን ሰዎች ‘መልካም ሥራቸውን’ ማለትም ለሌሎች የሚያደርጉትን መልካም ነገር ማየት እንዲችሉ ብርሃናቸውን እንዲያበሩ አበረታቷቸዋል። እንዲህ ማድረጋቸው “በሰዎች ፊት” መንፈሳዊ ብርሃን ለማብራት የሚያስችላቸው ሲሆን ይህም ለመላው የሰው ዘር ጥቅም ያስገኛል። (ማቴዎስ 5:14-16⁠ን አንብብ።) በዛሬው ጊዜ ለሌሎች መልካም በማድረግና ምሥራቹን “በዓለም ዙሪያ” ማለትም “ለሕዝብ ሁሉ” በመስበኩ ሥራ በመካፈል ብርሃናችንን ማብራት እንችላለን። (ማቴ. 26:13፤ ማር. 13:10) ይህ እንዴት ያለ ልዩ መብት ነው!

  • ከሰዎች ጋር ምን ዓይነት ግንኙነት ሊኖረን ይገባል?
    መጠበቂያ ግንብ—2008 | ግንቦት 15
    • 15. የምናከናውናቸው መልካም ‘ሥራዎች’ ሰዎች ምን እንዲያደርጉ ሊያነሳሷቸው ይችላሉ?

      15 ኢየሱስ ብርሃን ስለማብራት ከተናገረ በኋላ ደቀ መዛሙርቱን “እንደዚሁም ሰዎች መልካሙን ሥራችሁን አይተው በሰማይ ያለውን አባታችሁን እንዲያከብሩ ብርሃናችሁ በሰዎች ፊት ይብራ” ብሏቸዋል። መልካም ‘ሥራችንን’ የተመለከቱ አንዳንዶች የአምላክ አገልጋዮች በመሆን እሱን ‘አክብረዋል።’ ይህን ማወቃችን “እንደ ከዋክብት በዓለም ሁሉ [ማብራታችንን]” እንድንቀጥል የሚያበረታታ ነው!—ፊልጵ. 2:15

      16. “የዓለም ብርሃን” ለመሆን ምን ማድረግ ይኖርብናል?

      16 “የዓለም ብርሃን” ለመሆን ስለ አምላክ መንግሥት በመስበኩና ደቀ መዛሙርት በማድረጉ ሥራ መካፈል ይኖርብናል። ይሁን እንጂ እንዲህ ማድረጉ ብቻ አይበቃም። ሐዋርያው ጳውሎስ “እንደ ብርሃን ልጆች ኑሩ፤ የብርሃኑ ፍሬ በበጎነት፣ በጽድቅና በእውነት ሁሉ ዘንድ ነውና” በማለት ጽፏል። (ኤፌ. 5:8, 9) ላቅ ካሉት የአምላክ የአቋም ደረጃዎች ጋር ምንጊዜም ተስማምተን በመኖር ምሳሌ መሆን ይኖርብናል። “ምንም እንኳ ክፉ እንደምትሠሩ አድርገው ቢያሟችሁም ለፍርድ በሚመጣበት ጊዜ መልካሙን ሥራችሁን ዐይተው እግዚአብሔርን እንዲያከብሩ፣ በአሕዛብ መካከል በመልካም ሕይወት ኑሩ” የሚለውን የሐዋርያው ጴጥሮስን ምክር ተግባራዊ ማድረግ ይኖርብናል። (1 ጴጥ. 2:12) ይሁን እንጂ በሁለት ክርስቲያኖች መካከል አለመግባባት ቢፈጠር ምን መደረግ ይኖርበታል?

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ