-
ከጸሎት ናሙናው ጋር ተስማምቶ መኖር—ክፍል 1መጠበቂያ ግንብ—2015 | ሰኔ 15
-
-
“በሰማያት የምትኖር አባታችን ሆይ”
4. “አባታችን ሆይ” የሚለው አገላለጽ ምን ያስታውሰናል? ምድራዊ ተስፋ ያላቸው ክርስቲያኖች ይሖዋን “አባት” ብለው መጥራት የሚችሉት ከምን አንጻር ነው?
4 በጸሎት ናሙናው ላይ “አባቴ ሆይ” ሳይሆን “አባታችን ሆይ” መባሉ እርስ በርስ ከልብ በሚዋደድ “የወንድማማች ማኅበር” ውስጥ እንደታቀፍን ያስታውሰናል። (1 ጴጥ. 2:17) ይህ እንዴት ያለ ውድ መብት ነው! አምላክ እንደ ልጆቹ አድርጎ የወሰዳቸውና ሰማያዊ ሕይወት የሚያገኙ ቅቡዓን ክርስቲያኖች ይሖዋን “አባት” ብለው የመጥራት ልዩ የሆነ መብት አላቸው። (ሮም 8:15-17) በምድር ላይ ለዘላለም የመኖር ተስፋ ያላቸው ክርስቲያኖችም ቢሆኑ ይሖዋን “አባት” ብለው መጥራት ይችላሉ። ይሖዋ ሕይወት ሰጪያቸው ከመሆኑም ሌላ ለሁሉም እውነተኛ አምላኪዎቹ የሚያስፈልጋቸውን ነገር በፍቅር ተነሳስቶ ያቀርብላቸዋል። ምድራዊ ተስፋ ያላቸው እነዚህ የአምላክ አገልጋዮች ፍጽምና ደረጃ ላይ ከደረሱና በመጨረሻው ፈተና ታማኝ መሆናቸውን ካረጋገጡ በኋላ “የአምላክ ልጆች” ተብለው ይጠራሉ።—ሮም 8:21፤ ራእይ 20:7, 8
-
-
ከጸሎት ናሙናው ጋር ተስማምቶ መኖር—ክፍል 1መጠበቂያ ግንብ—2015 | ሰኔ 15
-
-
“ስምህ ይቀደስ”
7. የአምላክ ሕዝቦች ምን መብት አለን? ይህስ ምን ኃላፊነት ያስከትልብናል?
7 የአምላክን የግል ስም ከማወቅም አልፈን “ለስሙ የሚሆኑ ሰዎች” በመሆን በስሙ መጠራታችን ምንኛ ታላቅ መብት ነው። (ሥራ 15:14፤ ኢሳ. 43:10) በሰማይ የሚኖረውን አባታችንን “ስምህ ይቀደስ” ብለን እንለምነዋለን። እንዲህ ያለ ልመና ማቅረብህ፣ ቅዱስ የሆነውን የይሖዋን ስም የሚያስነቅፍ ነገር ላለመናገር ወይም ላለማድረግ እንዲረዳህ እሱን ለመጠየቅ ሊያነሳሳህ ይችላል። በመጀመሪያው መቶ ዘመን እንደነበሩት የሚሰብኩትን ነገር ተግባራዊ ያላደረጉ ክርስቲያኖች መሆን እንደማንፈልግ የታወቀ ነው። ሐዋርያው ጳውሎስ “በእናንተ ምክንያት የአምላክ ስም በአሕዛብ መካከል ይሰደባል” በማለት ጽፎላቸዋል።—ሮም 2:21-24
8, 9. የይሖዋ ስም እንዲቀደስ ማድረጋቸው የሚያሳስባቸውን ክርስቲያኖች ይሖዋ እንዴት እንደሚባርክ የሚያሳይ ምሳሌ ስጥ።
8 የአምላክ ስም እንዲቀደስ ማድረግ እንፈልጋለን። በኖርዌይ የምትኖር አንዲት እህት ባሏ ሲሞት ከሁለት ዓመት ልጇ ጋር ብቻዋን ቀረች። “በሕይወቴ ውስጥ በጣም ከባድ ወቅት ነበር” በማለት ተናግራለች። አክላም እንዲህ ብላለች፦ “ስሜታዊ ሆኜ ሚዛኔን እንዳልስት ይሖዋ ጥንካሬ እንዲሰጠኝ በየዕለቱ እንዲያውም በየሰዓቱ እጸልይ ነበር፤ ይህንንም የማደርገው ጥበብ የጎደለው ውሳኔ በመወሰኔ ወይም ታማኝነቴን በማጉደሌ ሰይጣን ይሖዋን የሚነቅፍበት ነገር እንዳያገኝ ስል ነው። የይሖዋ ስም እንዲቀደስ ማድረግ እፈልጋለሁ፤ ልጄም አባቱን በገነት እንዲያገኝ እመኛለሁ።”—ምሳሌ 27:11
9 ይሖዋ እንዲህ ላሉ ከራስ ወዳድነት ነፃ ለሆኑ ጸሎቶች ምላሽ ይሰጣል? በሚገባ። ይህች እህት አሳቢ ከሆኑ የእምነት ባልንጀሮቿ ጋር አዘውትራ ጊዜ በማሳለፏ ድጋፍ ማግኘት ችላለች። ከአምስት ዓመት በኋላ አንድ የጉባኤ ሽማግሌ አገባች። አሁን ልጇ 20 ዓመቱ ሲሆን የተጠመቀ የይሖዋ ምሥክር ነው። “ባለቤቴ ልጄን ሳሳድግ ስላገዘኝ በጣም ደስተኛ ነኝ” ብላለች።
10. የአምላክ ስም ሙሉ በሙሉ እንዲቀደስ ምን ያስፈልጋል?
10 የአምላክ ስም ሙሉ በሙሉ እንዲቀደስና ከደረሰበት ነቀፋ ሁሉ ነፃ እንዲሆን ምን ያስፈልጋል? ይሖዋ የእሱን ሉዓላዊነት ሆን ብለው የሚቃወሙትን ሁሉ ማጥፋት ያስፈልገዋል። (ሕዝቅኤል 38:22, 23ን አንብብ።) ከዚያም የሰው ዘር ቀስ በቀስ ወደ ፍጽምና ይደርሳል። የማሰብ ችሎታ ያላቸው ፍጥረታት በሙሉ የይሖዋን ስም የሚያስቀድሱበትን ጊዜ ለማየት ምንኛ እንጓጓለን! በመጨረሻም አፍቃሪው ሰማያዊ አባታችን “ለሁሉም ሁሉንም ነገር” ይሆናል።—1 ቆሮ. 15:28
-