-
ጭንቀት የእምነት ማነስን ያመለክታል?ንቁ!—2004 | ሐምሌ 8
-
-
የመጽሐፍ ቅዱስ አመለካከት
ጭንቀት የእምነት ማነስን ያመለክታል?
“መጨነቅ ተገቢ አይደለም።” በ20ኛው መቶ ዘመን መጀመሪያ ላይ አንድ ቄስ በዚህ ርዕስ ባቀረቡት ጽሑፍ ለቁሳዊ ነገሮች መጨነቅ ስህተት ብቻ ሳይሆን “ከባድ ኃጢአት” እንደሆነም ተናግረዋል። በቅርቡ ደግሞ አንድ ዘጋቢ ስጋትንና ጭንቀትን ስለመቋቋም ሲጽፍ “ጭንቀት በአምላክ እንደማንታመን ያሳያል” ብሏል።
ከላይ የተጠቀሱት ሁለቱ ጸሐፊዎች ከዚህ ድምዳሜ ላይ የደረሱት ኢየሱስ በተራራ ስብከቱ ላይ “አትጨነቁ” በማለት የተናገረውን ተንተርሰው ነው። (ማቴዎስ 6:25) በዛሬው ጊዜ ብዙ ሰዎች በጭንቀት ስለሚጠቁ አንድ ክርስቲያን በጭንቀት ከተዋጠ የጥፋተኝነት ስሜት ሊያድርበት ይገባል? ብለን እንጠይቅ ይሆናል። መጨነቅ የእምነት ማነስን ያመለክታል?
-
-
ጭንቀት የእምነት ማነስን ያመለክታል?ንቁ!—2004 | ሐምሌ 8
-
-
አምላክ የሚያስፈልገንን ያውቃል
ቅዱሳን ጽሑፎች በዕለታዊ ሕይወታችን በሚያጋጥመን ጭንቀትና እንደ ኃጢአት በሚቆጠረው እምነት ማጣት መካከል ያለውን ልዩነት እንድናስተውል ይረዱናል። ዕለታዊ ጭንቀት ወይም በሰብአዊ ድካም የተነሳ የሚያጋጥም ድንገተኛ የእምነት ማጣት ከክፉና ደንዳና ልብ ከሚመነጨው በአምላክ ላይ ፈጽሞ እምነት ከማጣት ጋር አንድ ተደርጎ መታየት አይኖርበትም። በመሆኑም ክርስቲያኖች አልፎ አልፎ ጭንቀት ቢያጋጥማቸው በጥፋተኝነት ስሜት መዋጥ የለባቸውም።
ይሁንና ሕይወታችንን እስኪቆጣጠረው ድረስ ከልክ በላይ በጭንቀት ላለመዋጥ መጠንቀቅ ያስፈልገናል። በመሆኑም ኢየሱስ “ስለ ኑሮአችሁ ምን እንበላለን? ምን እንጠጣለን? ምንስ እንለብሳለን? በማለት አትጨነቁ” ሲል ጥበብ የተሞላበት ሐሳብ ተናግሯል። ኢየሱስ ከዚህ በማስከተል የሚከተሉትን የሚያጽናኑ ቃላት ተናግሯል:- “የሰማዩ አባታችሁም እነዚህ ሁሉ ለእናንተ እንደሚያስፈልጓችሁ ያውቃል። ከሁሉ አስቀድማችሁ ግን የእግዚአብሔርን መንግሥትና ጽድቁን እሹ፤ እነዚህ ሁሉ ይጨመሩላችኋል።”—ማቴዎስ 6:25-33
-