የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • jy ምዕ. 32 ገጽ 78-ገጽ 79 አን. 7
  • በሰንበት የተፈቀደው ምንድን ነው?

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • በሰንበት የተፈቀደው ምንድን ነው?
  • ኢየሱስ—መንገድ፣ እውነት፣ ሕይወት
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • በሰንበት የተፈቀደው ምንድን ነው?
    እስከ ዛሬ ከኖሩት ሁሉ የሚበልጠው ታላቅ ሰው
  • በሰንበት እሸት መቅጠፍ
    ኢየሱስ—መንገድ፣ እውነት፣ ሕይወት
  • ክርስቲያኖች ሰንበትን ማክበር ይኖርባቸዋል?
    የመጽሐፍ ቅዱስ ጥያቄዎችና መልሶቻቸው
  • በሰንበት ቀን እሸት መቅጠፍ
    እስከ ዛሬ ከኖሩት ሁሉ የሚበልጠው ታላቅ ሰው
ለተጨማሪ መረጃ
ኢየሱስ—መንገድ፣ እውነት፣ ሕይወት
jy ምዕ. 32 ገጽ 78-ገጽ 79 አን. 7
ኢየሱስ እጁ የሰለለን ሰው ሊፈውስ ሲል

ምዕራፍ 32

በሰንበት የተፈቀደው ምንድን ነው?

ማቴዎስ 12:9-14 ማርቆስ 3:1-6 ሉቃስ 6:6-11

  • በሰንበት የአንድን ሰው እጅ ፈወሰ

በሌላ ሰንበት ኢየሱስ ወደ አንድ ምኩራብ ሄደ፤ ቦታው በገሊላ ሳይሆን አይቀርም። በዚያም ቀኝ እጁ የሰለለ አንድ ሰው ተመለከተ። (ሉቃስ 6:6) ጸሐፍትና ፈሪሳውያን ኢየሱስን በትኩረት እየተከታተሉት ነው። ለምን? “በሰንበት መፈወስ በሕግ ተፈቅዷል?” በማለት ያቀረቡት ጥያቄ ዓላማቸው ምን እንደሆነ በግልጽ ያሳያል።—ማቴዎስ 12:10

የሃይማኖት መሪዎቹ በሰንበት ሕክምና መስጠት የሚቻለው ለሕይወት የሚያሰጋ ሁኔታ ከተፈጠረ ብቻ እንደሆነ ያምናሉ። ለምሳሌ ያህል፣ አንድ ሰው ወለም ቢለው አጥንቱን ቦታው ማስገባት ወይም በጨርቅ መጠቅለል የተከለከለ ነው፤ ምክንያቱም እነዚህ ሁኔታዎች ለሕይወት የሚያሰጉ አይደሉም። በግልጽ ለማየት እንደሚቻለው ጸሐፍትና ፈሪሳውያን ለኢየሱስ ይህን ጥያቄ ያቀረቡለት የዚህ ሰው ሥቃይ ስላስጨነቃቸው አይደለም። ከዚህ ይልቅ ኢየሱስን የሚከስሱበት ሰበብ ለማግኘት ስለፈለጉ ነው።

ኢየሱስ ግን አስተሳሰባቸው ጠማማ እንደሆነ አውቋል። ‘በሰንበት መሥራትን የሚከለክለው ሕግ ተጣሰ’ የሚባለው መቼ እንደሆነ ያላቸው አመለካከት ከቅዱስ ጽሑፉ የራቀና ሚዛናዊነት የጎደለው እንደሆነ ተገንዝቦ ነበር። (ዘፀአት 20:8-10) መልካም ሥራ በመሥራቱ ከዚህ ቀደም እንዲህ ያለ የተሳሳተ ትችት ተሰንዝሮበታል። ስለዚህ ኢየሱስ እጁ የሰለለበትን ሰው “ተነሳና ወደ መሃል ና” ብሎ በመጋበዝ በጉዳዩ ላይ ፊት ለፊት ለመነጋገር የሚያስችል መድረክ አመቻቸ።—ማርቆስ 3:3

ኢየሱስ ወደ ጸሐፍትና ፈሪሳውያን ዞር ብሎ “ከእናንተ መካከል አንድ በግ ያለው ሰው ቢኖርና በሰንበት ቀን ጉድጓድ ውስጥ ቢገባበት በጉን ጎትቶ የማያወጣው ይኖራል?” ብሎ ጠየቃቸው። (ማቴዎስ 12:11) በግ በገንዘብ የሚገኝ ንብረት በመሆኑ እስከሚቀጥለው ቀን ድረስ እዚያው ጉድጓድ ውስጥ አይተዉትም፤ ምክንያቱም እዚያ እያለ ቢሞት ኪሳራ ይሆንባቸዋል። ከዚህም ሌላ መጽሐፍ ቅዱስ “ጻድቅ የቤት እንስሳቱን ይንከባከባል” ይላል።—ምሳሌ 12:10

ቀጥሎም ኢየሱስ የሚከተለውን ምክንያታዊነት የተንጸባረቀበት ንጽጽር ተጠቀመ፦ “ታዲያ ሰው ከበግ እጅግ አይበልጥም? ስለዚህ በሰንበት መልካም ነገር ማድረግ ተፈቅዷል።” (ማቴዎስ 12:12) ከዚህ አንጻር ኢየሱስ ሰውየውን መፈወሱ የሰንበትን ሕግ መጣስ አይሆንበትም። የሃይማኖት መሪዎቹ ይህን ምክንያታዊነትና ርኅራኄ የተሞላበት አነጋገር ማስተባበል ስላልቻሉ ዝም አሉ።

ኢየሱስ በተዛባ አስተሳሰባቸው በማዘን በዙሪያው ያሉትን በብስጭት ተመለከተ። ከዚያም ሰውየውን “እጅህን ዘርጋ” አለው። (ማቴዎስ 12:13) ሰውየው የሰለለ እጁን ሲዘረጋ ተፈወሰ። ግለሰቡ በዚህ እንደሚደሰት ጥርጥር የለውም፤ ይሁንና ኢየሱስን ለማጥመድ የሞከሩት ሰዎች ምን ተሰማቸው?

የአይሁድ መሪዎች ኢየሱስን ለመግደል ተማከሩ

ፈሪሳውያን የሰውየው እጅ በመዳኑ መደሰት ሲገባቸው “ወዲያው ከሄሮድስ ሥርወ መንግሥት ደጋፊዎች ጋር በመሰብሰብ [ኢየሱስን] እንዴት እንደሚገድሉት መመካከር ጀመሩ።” (ማርቆስ 3:6) ይህ የፖለቲካ ቡድን፣ ሰዱቃውያን የሚባሉትን የሃይማኖት ሰዎች ያቀፈ ሳይሆን አይቀርም። እንደ ወትሮው ቢሆን ሰዱቃውያንና ፈሪሳውያን እርስ በርስ አይስማሙም፤ አሁን ግን ኢየሱስን በመቃወም ግንባር ፈጠሩ።

  • ኢየሱስና የሃይማኖት መሪዎቹ ፊት ለፊት እንዲነጋገሩ መንገድ የከፈተው ሁኔታ ምንድን ነው?

  • የሃይማኖት መሪዎቹ የሰንበትን ሕግ በተመለከተ ምን የተሳሳተ አመለካከት አላቸው?

  • ኢየሱስ፣ ስለ ሰንበት በዘመኑ የነበረው አመለካከት የተሳሳተ መሆኑን በዘዴ ያሳየው እንዴት ነው?

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ