የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • ክርስቲያን ሴቶች ከፍተኛ ግምትና አክብሮት ሊሰጣቸው ይገባል
    መጠበቂያ ግንብ—1995 | ሐምሌ 15
    • 10 ፍቺን በተመለከተ ኢየሱስ “ሰው በሆነው ምክንያት ሁሉ ሚስቱን ሊፈታ ተፈቅዶለታልን?” የሚል ጥያቄ ተጠይቆ ነበር። በማርቆስ ዘገባ መሠረት ኢየሱስ “[ያለ ዝሙት ምክንያት] ሚስቱን ፈትቶ ሌላ የሚያገባ ሁሉ በእርሷ ላይ ያመነዝራል፤ እርስዋም ባልዋን ፈትታ ሌላ ብታገባ ታመነዝራለች” አላቸው። (ማርቆስ 10:10–12፤ ማቴዎስ 19:3, 9) እነዚህ በቀላል አነጋገር የተገለጹ ቃላት ለሴቶች አክብሮትን ያሳያሉ። እንዴት?

  • ክርስቲያን ሴቶች ከፍተኛ ግምትና አክብሮት ሊሰጣቸው ይገባል
    መጠበቂያ ግንብ—1995 | ሐምሌ 15
    • 12. “በእርሷ ላይ ያመነዝራል” በሚሉት ቃላት ኢየሱስ ያስተዋወቀው ሐሳብ ምን ነበር?

      12 በሁለተኛ ደረጃ “በእርሷ ላይ ያመነዝራል” በሚሉት ቃላት በሚጠቀምበት ወቅት ኢየሱስ በረቢ ፍርድ ቤቶች የማይታወቅ አንድ አመለካከት ማለትም ባል በሚስቱ ላይ ያመነዝራል የሚል አመለካከት አስተዋውቋል። ዘ ኤክስፖዚተርስ ባይብል ኮሜንታሪ የተባለው መጽሐፍ የሚከተለውን ማብራሪያ ይሰጣል፦ “የአይሁድ እምነት ተከታዮች የነበሩ ረቢዎች አንዲት ሴት ታማኝነቷን በማጉደል በባሏ ላይ ታመነዝራለች፤ አንድ ወንድ ከሌላ ሰው ሚስት ጋር የግብረ ሥጋ ግንኙነት ቢያደርግ በራሱ ላይ ምንዝር ይፈጽማል። ይሁን እንጂ አንድ ወንድ የፈለገውን ነገር ቢያደርግ በጭራሽ በሚስቱ ላይ ምንዝር ፈጸመ ሊባል አይችልም ይሉ ነበር። ኢየሱስ ግን ባል የሚስትን ያህል የሥነ ምግባር ግዴታ እንዳለበት ሲገልጽ የሴትን ደረጃና ክብር ከፍ አድርጓል።”

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ