-
አዎንታዊ አመለካከት ይዘን መቀጠል የምንችለው እንዴት ነው?መጠበቂያ ግንብ—2014 | መጋቢት 15
-
-
8, 9. (ሀ) ድሃዋ መበለት የነበረችበት ሁኔታ ምን ይመስላል? (ለ) ይህች መበለት ምን ዓይነት አሉታዊ ስሜት አድሮባት ሊሆን ይችላል?
8 ኢየሱስ በኢየሩሳሌም በሚገኘው ቤተ መቅደስ ሆኖ አንዲትን መበለት እየተመለከተ ነው። ይህች መበለት የተወችው ምሳሌ የአቅም ገደብ ቢኖርብንም ስለ ራሳችን አዎንታዊ አመለካከት እንድንይዝ ይረዳናል። (ሉቃስ 21:1-4ን አንብብ።) እስቲ የዚህችን መበለት ሁኔታ እንመልከት። ይህች ሴት ባሏን በሞት ማጣቷ ያስከተለባት ሐዘን ሳያንሳት መበለቶችን ከመርዳት ይልቅ እንደ እሷ ያሉ ምስኪኖችን ‘ቤት የሚያራቁቱ’ የሃይማኖት መሪዎች የሚያደርሱባትን እንግልት ችላ መኖር ነበረባት። (ሉቃስ 20:47) ይህች ሴት በጣም ድሃ ስለነበረች ለቤተ መቅደሱ መስጠት የምትችለው አንድ የቀን ሠራተኛ በጥቂት ደቂቃዎች ውስጥ የሚያገኘውን ገቢ ያህል ብቻ ነበር።
9 መበለቷ ሁለት ትናንሽ ሳንቲሞችን ይዛ ወደ ቤተ መቅደሱ አደባባይ ስትሄድ ምን ተሰምቷት ሊሆን እንደሚችል አስበው። ባሏ በሕይወት በነበረበት ወቅት ትሰጥ ከነበረው አንጻር አሁን የምትሰጠው ምን ያህል ትንሽ እንደሆነ እያሰበች ይሆን? ከእሷ በፊት ያሉት ሰዎች የሚሰጡትን ብዛት ያለው ገንዘብ ስትመለከት ትሸማቀቅ ምናልባትም የእሷ ስጦታ እዚህ ግባ የማይባል እንደሆነ ይሰማት ይሆን? እንዲህ ዓይነት ስሜት አድሮባት ሊሆን ቢችልም እውነተኛውን አምልኮ ለመደገፍ አቅሟ የፈቀደውን ከማድረግ ወደኋላ አላለችም።
-
-
አዎንታዊ አመለካከት ይዘን መቀጠል የምንችለው እንዴት ነው?መጠበቂያ ግንብ—2014 | መጋቢት 15
-
-
11. ከመበለቷ ታሪክ ምን ትምህርት ማግኘት ትችላለህ?
11 ለይሖዋ መስጠት የምትችለው ነገር ባለህበት ሁኔታ ላይ የተመካ ሊሆን ይችላል። በዕድሜ መግፋት ወይም በጤና እክል ሳቢያ አንዳንዶች ምሥራቹን በመስበኩ ሥራ ላይ የሚያሳልፉት ጊዜ በጣም ትንሽ ይሆናል። ታዲያ እነዚህ ክርስቲያኖች በስብከቱ ሥራ ያሳለፉት ሰዓት ሪፖርት ለማድረግ የሚበቃ እንዳልሆነ ሊሰማቸው ይገባል? በሌላ በኩል ደግሞ ከባድ የአቅም ገደብ ባይኖርብህም እንኳ የአምላክ ሕዝቦች በእሱ አገልግሎት ከሚያሳልፉት ሰዓት አንጻር የአንተ አስተዋጽኦ ከቁብ የሚቆጠር እንዳልሆነ ይሰማህ ይሆናል። ያም ቢሆን ይሖዋ በእሱ አገልግሎት የምናከናውነውን እያንዳንዱን ነገር በተለይም በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ሆነን የምናደርገውን ነገር ልብ የሚል ከመሆኑም በላይ ከፍ አድርጎ እንደሚመለከተው ከድሃዋ መበለት ታሪክ መማር እንችላለን። እስቲ ባለፈው ዓመት በይሖዋ አገልግሎት ስላሳለፍከው ጊዜ መለስ ብለህ አስብ። አገልግሎትህን ለማከናወን ስትል ለየት ያለ መሥዋዕት የከፈልክበት ሰዓት አለ? ከሆነ ይሖዋ በዚያ ሰዓት ያከናወንከውን አገልግሎት ከፍ አድርጎ እንደሚመለከተው እርግጠኛ መሆን ትችላለህ። እንደ ድሃዋ መበለት በይሖዋ አገልግሎት የተቻለህን ሁሉ እያደረግህ ከሆነ ‘በእምነት ውስጥ እየተመላለስክ’ መሆንህን ለማመን የሚያበቃ ምክንያት አለህ።
-