የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • ተስፋ የተሰጠበት ልጅ
    ኢየሱስ—መንገድ፣ እውነት፣ ሕይወት
    • ይህ ከሆነ በኋላ ከአንድ ወር የሚበልጥ ጊዜ አለፈ፤ ኢየሱስም 40 ቀን ሞላው። ታዲያ በዚህ ጊዜ ወላጆቹ ወዴት ይወስዱታል? ካረፉበት ቦታ በስተ ሰሜን ጥቂት ኪሎ ሜትሮች ርቀት ላይ ወደሚገኘው በኢየሩሳሌም ወዳለው ቤተ መቅደስ ወሰዱት። በሕጉ መሠረት ወንድ ልጅ ከተወለደ ከ40 ቀናት በኋላ እናትየዋ ወደ ቤተ መቅደሱ ሄዳ የመንጻት መሥዋዕት ማቅረብ ይኖርባታል።—ዘሌዋውያን 12:4-8

      ማርያምም ያደረገችው ይህንኑ ነው። ለመሥዋዕት ይዛ የመጣችው ሁለት ትናንሽ ወፎችን ነው። ይህም የዮሴፍንና የማርያምን የኑሮ ደረጃ ይጠቁማል። ሕጉ እንደሚያዝዘው ለመሥዋዕት መቅረብ ያለበት የበግ ጠቦትና አንድ ወፍ ነው። ሆኖም እናቲቱ የበግ ጠቦት ለማቅረብ አቅሟ የማይፈቅድላት ከሆነ ሁለት ዋኖሶች ወይም ሁለት የርግብ ጫጩቶች ማቅረብ ትችላለች። ማርያምም አቅሟ የፈቀደላትና ያቀረበችው ይህንን ነው።

      “የሚነጹበት ጊዜ ሲደርስ”

      ዮሴፍና ማርያም፣ የመንጻት መሥዋዕት ለማቅረብ ሕፃኑን ኢየሱስን ይዘው ወደ ቤተ መቅደሱ መጡ

      እስራኤላውያን ሴቶች፣ ልጅ ሲወልዱ በሕጉ መሠረት ለተወሰነ ጊዜ ያህል ርኩስ እንደሆኑ ተደርገው ይቆጠራሉ። ይህ ጊዜ ሲያበቃ ለመንጻት ሲሉ የሚቃጠል መሥዋዕት ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል። ይህም ፍጽምና የጎደለውና ኃጢአተኛ የሆነ ልጅ መወለዱን እንዲያስታውሱ ያደርጋል። እርግጥ ሕፃኑ ኢየሱስ ፍጹምና ቅዱስ ነው። (ሉቃስ 1:35) ያም ቢሆን “የሚነጹበት ጊዜ ሲደርስ” ሕጉ በሚያዘው መሠረት ማርያምና ዮሴፍ ሕፃኑን ወደ ቤተ መቅደሱ “ይዘውት መጡ።”—ሉቃስ 2:22

  • ተስፋ የተሰጠበት ልጅ
    ኢየሱስ—መንገድ፣ እውነት፣ ሕይወት
አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ