የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • የጌታ እራት ለአንተ ትልቅ ትርጉም አለው
    መጠበቂያ ግንብ—2003 | ሚያዝያ 1
    • “ቂጣውንም አንሥቶ አመሰገነ ቆርሶም ሰጣቸውና:- ይህ ስለ እናንተ የሚሰጥ ሥጋዬ ነው፤ ይህን ለመታሰቢያዬ አድርጉት አለ።”​—⁠ሉቃስ 22:19

      ኢየሱስ ቂጣውን አንስቶ “ይህ ስለ እናንተ የሚሰጥ ሥጋዬ ነው” ብሎ ሲናገር እርሾ ያልገባበት ቂጣ ‘ስለ ዓለም ሕይወት የሚሰጠውን’ ኃጢአት የሌለበትን ሰብዓዊ አካሉን እንደሚያመለክት መግለጹ ነበር። (ዮሐንስ 6:51) የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስን ጨምሮ አንዳንድ መጽሐፍ ቅዱሶች ይህንን ጥቅስ “ይህ ሥጋዬ ነው [በግሪክኛ ኤስቲን]” ብለው ቢተረጉሙትም በቴየር የተዘጋጀው ግሪክ-ኢንግሊሽ ሌክሲከን ኦቭ ዘ ኒው ቴስታመንት ይህ ግስ በአብዛኛው “ማመልከት” የሚል ትርጉም እንዳለው ይገልጻል። ቃሉ አንድን ነገር ለማመልከት የቆመ ምሳሌያዊ መግለጫ የሚል ትርጉም አለው።​—⁠ማቴዎስ 26:26 አዲሱ መደበኛ ትርጉም ከማጥኛ ጽሑፍ ጋር የግርጌ ማስታወሻ ተመልከት

  • የጌታ እራት ለአንተ ትልቅ ትርጉም አለው
    መጠበቂያ ግንብ—2003 | ሚያዝያ 1
    • [በገጽ 5, 6 ላይ የሚገኝ ሣጥን/ሥዕል]

      “ይህ ሥጋዬ ነው” ወይስ “ይህ ማለት ሥጋዬ ነው”?

      ኢየሱስ “እኔ የበጎች በር ነኝ” ወይም “እውነተኛ የወይን ግንድ እኔ ነኝ” ብሎ ሲናገር ቃል በቃል በር ወይም የወይን ግንድ ነው ብለን አናስብም። (ዮሐንስ 10:7፤ 15:1) በተመሳሳይም መጽሐፍ ቅዱስ “ይህ ጽዋ . . . አዲስ ኪዳን ነው” ሲል ጽዋው ራሱ ቃል በቃል አዲስ ኪዳን እንደሆነ አድርገን አናስብም። ልክ እንደዚያው ሁሉ ኢየሱስ ቂጣው ሥጋው ‘እንደሆነ’ ሲናገር ቂጣው ሥጋውን እንደሚያመለክት መናገሩ እንደሆነ ምንም ጥርጥር የለውም። በመሆኑም በቻርልስ ቢ ዊሊያምስ የተዘጋጀው መጽሐፍ ቅዱስ ጥቅሱን “ይህ ሥጋዬን ያመለክታል” በማለት ተርጉሞታል።​—⁠ሉቃስ 22:19, 20

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ