-
እጅግ አዝኖ እያለ ያቀረበው ጸሎትኢየሱስ—መንገድ፣ እውነት፣ ሕይወት
-
-
ኢየሱስ እንደ ወንጀለኛ ተቆጥሮ የሚሞት መሆኑ በአባቱ ስም ላይ የሚያመጣው ነቀፋ በጣም አሳስቦታል። ይሖዋም የልጁን ጸሎት በመስማት መልአክ ልኮ አበረታታው። ያም ቢሆን ኢየሱስ ወደ አባቱ ምልጃ ማቅረቡን አላቆመም፤ እንዲያውም “ከበፊቱ ይበልጥ አጥብቆ መጸለዩን ቀጠለ።” ኢየሱስ በከፍተኛ ጭንቀት ተውጧል። በኢየሱስ ጫንቃ ላይ ታላቅ ኃላፊነት ወድቋል! የእሱም ሆነ እምነት ያላቸው የሰው ልጆች የዘላለም ሕይወት ተስፋ የተመካው በእሱ ላይ ነው። ከጭንቀቱ የተነሳ ላቡ “መሬት ላይ እንደሚንጠባጠብ ደም” ሆነ።—ሉቃስ 22:44
-