-
የመጽሐፍ ቅዱስ መጽሐፍ ቁጥር 19—መዝሙር“ቅዱሳት መጻሕፍት ሁሉ” ትክክለኛና ጠቃሚ ናቸው፣ ጥራዝ 14
-
-
11 የመጽሐፉን ትክክለኛነት ለማረጋገጥ ከሁሉ የላቀው ጠንካራ ማስረጃ ከሞት የተነሳው ጌታ ኢየሱስ ሲሆን እርሱም ለደቀ መዛሙርቱ “‘በሙሴ ሕግ፣ በነቢያትና በመዝሙር መጻሕፍት ስለ እኔ የተጻፈው ሁሉ ይፈጸም ዘንድ ይገባል’ ብዬ የነገርኋችሁ ቃሌ ይህ ነው” ብሏቸዋል። እዚህ ላይ ኢየሱስ የዕብራይስጥ ቅዱሳን ጽሑፎችን በሙሉ፣ አይሁዳውያን በሚጠቀሙበትና ደቀ መዛሙርቱ ጠንቅቀው በሚያውቁት መንገድ ከፋፍሎ መጥቀሱ ነበር። የመዝሙር መጻሕፍት ሲል በሦስተኛው የቅዱሳን ጽሑፎች ክፍል ውስጥ የተካተቱትን መጻሕፍት በሙሉ ማመልከቱ ነበር፤ እነዚህ መጻሕፍት ሃጊዎግራፋ (ወይም ቅዱሳን ጽሑፎች) ተብለው የሚጠሩ ሲሆን ከዚህ ክፍል ውስጥ የመጀመሪያው መጽሐፍ መዝሙር ነው። ኢየሱስ ከላይ ያለውን ከመናገሩ ጥቂት ሰዓታት ቀደም ብሎ ወደ ኤማሁስ ይጓዙ ለነበሩት ሁለት ደቀ መዛሙርት ‘በቅዱሳት መጻሕፍት ስለ እርሱ የተጻፈውን [“ሁሉ፣” የ1954 ትርጉም] ባስረዳቸው’ ወቅት የተናገረው ሐሳብ ይህን ያረጋግጣል።—ሉቃስ 24:27, 44
-
-
የመጽሐፍ ቅዱስ መጽሐፍ ቁጥር 42—ሉቃስ“ቅዱሳት መጻሕፍት ሁሉ” ትክክለኛና ጠቃሚ ናቸው፣ ጥራዝ 16
-
-
31 ኢየሱስ በዘካርያስ 9:9 ላይ አስቀድሞ እንደተነገረው በአህያ ውርንጭላ ላይ ተቀምጦ ወደ ኢየሩሳሌም ሲገባ በዚያ የነበሩት ብዙ ሰዎች መዝሙር 118:26 በእሱ ላይ እንደተፈጸመ በመግለጽ በደስታ ተቀብለውታል። (ሉቃስ 19:35-38) ኢየሱስ ነቀፋ በሚያስከትል መንገድ እንደሚገደልና በኋላም ትንሣኤ እንደሚያገኝ በዕብራይስጥ ቅዱሳን መጻሕፍት ውስጥ በትንቢት የተነገሩት ስድስት ነጥቦች በሉቃስ መጽሐፍ ውስጥ በሁለት ቁጥሮች ተጠቃልለው ተቀምጠዋል። (ሉቃስ 18:32, 33፤ መዝ. 22:7፤ ኢሳ. 50:6፤ 53:5-7፤ ዮናስ 1:17) ኢየሱስ ከሞት ከተነሳ በኋላም የጠቅላላውን የዕብራይስጥ ቅዱሳን መጻሕፍት ጠቀሜታ ለደቀ መዛሙርቱ ጠበቅ አድርጎ ሲገልጽ እንዲህ ብሏል:- “‘ከእናንተ ጋር በነበርሁበት ጊዜ፣ “በሙሴ ሕግ፣ በነቢያትና በመዝሙር መጻሕፍት ስለ እኔ የተጻፈው ሁሉ ይፈጸም ዘንድ ይገባል” ብዬ የነገርኋችሁ ቃሌ ይህ ነው’ አላቸው። በዚህ ጊዜ ቅዱሳት መጻሕፍትን እንዲያስተውሉ አእምሮአቸውን ከፈተላቸው።” (ሉቃስ 24:44, 45) እንደ መጀመሪያዎቹ የኢየሱስ ክርስቶስ ደቀ መዛሙርት ሁሉ እኛም ሉቃስና የክርስቲያን ግሪክኛ ቅዱሳን መጻሕፍትን የጻፉት ሌሎች ሰዎች በትክክል ያብራሩትን የዕብራይስጥ ቅዱሳን መጻሕፍት ፍጻሜ በትኩረት መከታተላችን ተጨማሪ እውቀት እንድናገኝና እምነታችን እንዲጠናከር ያደርጋል።
-