-
በመንፈሳዊው ዓለም ውስጥ ያሉ ገዥዎችመጠበቂያ ግንብ—1995 | ሐምሌ 15
-
-
ኢየሱስ ተጠምቆ ብዙም ሳይቆይ ሰይጣን ዲያብሎስ በሚባል በዓይን በማይታይ በአንድ መንፈሳዊ ፍጡር ተፈተነ። መጽሐፍ ቅዱስ ከፈተናዎቹ መካከል አንዱን ሲጠቅስ “ደግሞ ዲያብሎስ እጅግ ረጅም ወደ ሆነ ተራራ [ኢየሱስን] ወሰደው፣ የዓለምንም መንግሥታት ሁሉ ክብራቸውንም” አሳየው በማለት ይናገራል። (ማቴዎስ 4:8) ከዚያም ሰይጣን “ይህ ሥልጣን ሁሉ ክብራቸውም ለእኔ ተሰጥቶአል ለምወደውም ለማንም እሰጠዋለሁና ለአንተ እሰጥሃለሁ፤ ስለዚህ አንተ በእኔ ፊት ብትሰግድ፣ ሁሉ ለአንተ ይሆናል አለው።”—ሉቃስ 4:6, 7
ሰይጣን በዚህ ዓለም በሚገኙ መንግሥታት ወይም መስተዳድሮች ላይ በሙሉ ሥልጣን እንዳለው ተናግሯል። ኢየሱስ ይህንን አባባል አስተባብሏልን? አላስተባበለም። እንዲያውም ኢየሱስ በሌላ ወቅት ሰይጣን “የዚህ ዓለም ገዥ” መሆኑን በመግለጽ ይህንን አባባል አጠናክሮታል።—ዮሐንስ 14:30
በመጽሐፍ ቅዱስ አገላለጽ መሠረት ሰይጣን ትልቅ ኃይል ያለው ክፉ መልአክ ነው። ክርስቲያኑ ሐዋርያ ጳውሎስ ሰይጣንን “ከክፋት መንፈሳውያን ሠራዊት” ጋር ከማዛመዱም በላይ እነዚህ ክፉ መንፈሳውያን ሠራዊት የዚህ የጨለማ ዓለም ገዥዎች መሆናቸውን ተናግሯል። (ኤፌሶን 6:11, 12) ከዚህም በላይ ሐዋርያው ዮሐንስ “ዓለምም በሞላው በክፉው” ተይዟል በማለት ገልጿል። (1 ዮሐንስ 5:19) የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል የሆነው የራእይ መጽሐፍ ሰይጣንን “ዓለሙንም ሁሉ የሚያስተው” በማለት ይገልጸዋል። (ራእይ 12:9) በተጨማሪም የራእይ መጽሐፍ ሰይጣንን በዘንዶ በመመሰል በዓለም ላይ ለሚገኘው የፖለቲካ ሥርዓት “ኃይሉንና ዙፋኑን ትልቅም ሥልጣን” እንደሰጠው በምሳሌ ገልጾታል።—ራእይ 13:2
በተጨማሪም የሰው ልጆችን ለመጉዳት እየተንቀሳቀሰ ያለ አንድ ክፉ ኃይል እንዳለ በዓለም ላይ እየተከሰቱ ያሉት ሁኔታዎች ያረጋግጣሉ። ሰብዓዊ መስተዳድሮች ሰላም ማስፈን ያቃታቸው በሌላ በምን ምክንያት ነው? ሰዎች እርስ በእርሳቸው እንዲጠላሉና እንዲተራረዱ የሚያነሳሳቸው ማን ሊሆን ይችላል? በእርስ በርስ ጦርነት በደረሰው እልቂትና ሞት ያዘኑ አንዲት የዓይን ምሥክር “ይህ አሠቃቂ ግፍ እንዴት ሊደርስ እንደቻለ አላውቅም። ይህ እንዲሁ ጥላቻ ብቻ አይደለም። እነዚህ ሰብዓዊ ፍጡራን እንዲጠፋፉ እየተጠቀመባቸው ያለው አንድ ክፉ መንፈስ ነው።”
-
-
በመንፈሳዊው ዓለም ውስጥ ያሉ ገዥዎችመጠበቂያ ግንብ—1995 | ሐምሌ 15
-
-
ሰይጣን እንዲገዛ የተፈቀደለት ለምንድን ነው?
በምድር ላይ ስለ መግዛት ሰይጣን ለኢየሱስ ምን እንዳለው ታስታውሳለህ? ሰይጣን “ይህ ሥልጣን ሁሉ . . . ለእኔ ተሰጥቶአል . . . ለአንተ እሰጥሃለሁ” በማለት ተናሯግል። (ሉቃስ 4:6) ሰይጣን ዲያብሎስ ሥልጣን የሚኖረው በአምላክ ፈቃድ ብቻ እንደሆነ ይህ ዓረፍተ ነገር ያሳያል። ይሁን እንጂ አምላክ ሰይጣንን የታገሠው ለምንድን ነው?
-