-
የመጽሐፍ ቅዱስ መጽሐፍ ቁጥር 42—ሉቃስ“ቅዱሳት መጻሕፍት ሁሉ” ትክክለኛና ጠቃሚ ናቸው፣ ጥራዝ 16
-
-
የሉቃስን ወንጌል የጻፈው፣ ንቁ አእምሮ ያለው ደግ ሰው ነው፤ እነዚህ ግሩም ባሕርያት የአምላክ መንፈስ ከሚሰጠው አመራር ጋር ተጣምረው ጸሐፊው ትክክለኛና ሕያው የሆነ ዘገባ እንዲያቀርብ አስችለውታል። በመግቢያው ላይ “እኔም በበኩሌ ሁሉን ከመሠረቱ በጥንቃቄ ከመረመርሁ በኋላ፣ ታሪኩን ቅደም ተከተሉን በጠበቀ ሁኔታ ልጽፍልህ መልካም ሆኖ ታየኝ” ሲል ተናግሯል። ጸሐፊው በዝርዝርና በጥንቃቄ ያሰፈረው ይህ ዘገባ አባባሉ እውነት መሆኑን በሚገባ ያረጋግጣል።—ሉቃስ 1:3
-
-
የመጽሐፍ ቅዱስ መጽሐፍ ቁጥር 42—ሉቃስ“ቅዱሳት መጻሕፍት ሁሉ” ትክክለኛና ጠቃሚ ናቸው፣ ጥራዝ 16
-
-
4 ሉቃስ ወንጌሉን የጻፈው መቼ ነው? በሐዋርያት ሥራ 1:1 ላይ የሚገኘው “ቀደም ባለው መጽሐፌ” የሚለው ሐሳብ እንደሚጠቁመው መጽሐፉን የጻፈው ሰው (ሉቃስ) ከዚያ በፊት ሌላ መጽሐፍ ማለትም ወንጌሉን ጽፏል። የሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ የተጠናቀቀው በ61 ከክርስቶስ ልደት በኋላ እንደሆነ ይገመታል፤ በዚህ ጊዜ ሉቃስ፣ ለቄሣር ይግባኝ ለማለት በሮም ሆኖ ጉዳዩን ይጠባበቅ ከነበረው ከጳውሎስ ጋር ነበር። በመሆኑም ሉቃስ ይህን የወንጌል ዘገባ የጻፈው፣ ጳውሎስ ሦስተኛ ሚስዮናዊ ጉዞውን ሲያጠናቅቅ ከፊልጵስዩስ አብሮት ከተመለሰ በኋላ ማለትም ከ56-58 ከክርስቶስ ልደት በኋላ ባለው ጊዜ ውስጥ ሳይሆን አይቀርም፤ ጳውሎስ ለቄሣር ይግባኝ ለማለት ወደ ሮም ከመወሰዱ በፊት በቂሣርያ ለሁለት ዓመታት እስር ቤት ቆይቷል። ሉቃስ በዚህ ወቅት በፓለስቲና ስለነበር የኢየሱስን ሕይወትና አገልግሎት በተመለከተ ‘ሁሉን ከመሠረቱ በጥንቃቄ ለመመርመር’ ጥሩ አጋጣሚ ነበረው። በመሆኑም የሉቃስ ወንጌል የተጻፈው ከማርቆስ ወንጌል ቀድሞ ይመስላል።
5 እርግጥ ነው፣ ሉቃስ ከ12ቱ ሐዋርያት አንዱ ስላልነበረና ምናልባትም አማኝ የሆነው ኢየሱስ ከሞተ በኋላ ስለሚሆን በወንጌሉ ውስጥ ያሰፈራቸው ክንውኖች በሙሉ ሲፈጸሙ አልተመለከተም። ይሁን እንጂ ጳውሎስ በሚስዮናዊነት ሲያገለግል የቅርብ ወዳጁ ነበር። (2 ጢሞ. 4:11፤ ፊል. 24) በመሆኑም በሉቃስ 22:19, 20 እና በ1 ቆሮንቶስ 11:23-25 ላይ ስለ ጌታ እራት የሚገልጸውን የሉቃስንና የጳውሎስን ዘገባ በማወዳደር፣ ሉቃስ ለጻፈው መጽሐፍ ሐሳብ ያገኘው ከጳውሎስ እንደነበረ መመልከት ይቻላል። ሉቃስ ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት የማቴዎስን ዘገባም አመሳክሮ ሊሆን ይችላል። ‘ሁሉን ከመሠረቱ በጥንቃቄ ለመመርመር’ በኢየሱስ ሕይወት ውስጥ የተከናወኑትን ነገሮች የተመለከቱ በርካታ ሰዎችን ለምሳሌ በሕይወት የነበሩትን ደቀ መዛሙርት እንዲሁም የኢየሱስን እናት ማርያምን በግል ቀርቦ ሊጠይቅ ይችል ነበር። አስተማማኝ የሆነ ዝርዝር ዘገባ ለማሰባሰብ ሲል ያልፈነቀለው ድንጋይ እንደማይኖር እርግጠኞች መሆን እንችላለን።
-