-
መጽሐፍ ቅዱስ እርስ በርሱ ይጋጫል?የመጽሐፍ ቅዱስ ጥያቄዎችና መልሶቻቸው
-
-
ነጥብ 5፦ በዋነኝነት ሥራውን ያከናወነው ሰው
ኢየሱስ በቅፍርናሆም በነበረበት ወቅት ቀርቦ ያነጋገረው ማን ነው? ማቴዎስ 8:5, 6 የመቶ አለቃው ራሱ ኢየሱስን ቀርቦ እንዳነጋገረው ይገልጻል፤ ሉቃስ 7:3 ግን የመቶ አለቃው የአይሁድ ሽማግሌዎችን ልኮ ልመናውን እንዳቀረበ ይናገራል። እነዚህ ሁለት ጥቅሶች የሚጋጩ ሊመስሉ ይችላሉ፤ ሆኖም በዋነኝነት ልመናውን ያቀረበው የመቶ አለቃው እንደሆነ፣ የአይሁድ ሽማግሌዎችን ግን አማላጅ አድርጎ ወደ ኢየሱስ እንደላካቸው ስንመለከት ሐሳቡ ግልጽ ይሆንልናል።
-
-
መጽሐፍ ቅዱስ እርስ በርሱ ይጋጫል?የመጽሐፍ ቅዱስ ጥያቄዎችና መልሶቻቸው
-
-
a ለምሳሌ ያህል፣ ኢንሳይክሎፒዲያ ብሪታኒካ ታጅ ማሃል “የተገነባው የሙጋል ንጉሠ ነገሥት በሆነው በሻህ ጃሀን” እንደሆነ ይናገራል። ይሁን እንጂ ግንባታውን ያከናወነው እሱ ራሱ አልነበረም፤ ምክንያቱም ኢንሳይክሎፒዲያው አክሎ እንደሚገልጸው “ከ20,000 የሚበልጡ ሠራተኞች ተቀጥረው” ግንባታውን አከናውነዋል።
-