-
የአምላክን ቃል መውደድ የሚያስገኛቸው ጥቅሞችመጠበቂያ ግንብ—1999 | ኅዳር 1
-
-
7. ኢየሱስ እርሱን ለመስማት ለመጡት ሰዎች ምን ምሳሌ ነገራቸው?
7 ለአምላክ ቃል ትክክለኛ አመለካከት የመያዝ አስፈላጊነት ኢየሱስ በተናገረው አንድ ምሳሌ ውስጥ ጎላ ተደርጎ ተገልጿል። ኢየሱስ በፍልስጤም ምድር ምሥራቹን ያውጅ በነበረበት ጊዜ ብዙ ሰዎች እርሱን ለመስማት ተሰበሰቡ። (ሉቃስ 8:1, 4) ይሁን እንጂ ለአምላክ ቃል ፍቅር የነበራቸው ሁሉም አልነበሩም። ብዙዎቹ እርሱን ለመስማት የመጡት ተዓምራት ለማየት ፈልገው ወይም ደግሞ በጣም አስገራሚ የነበረው የማስተማር ችሎታው ስላስደሰታቸው እንደነበር ምንም ጥርጥር የለውም። በመሆኑም ኢየሱስ ለተሰበሰበው ሕዝብ አንድ ምሳሌ ተናገረ:- “ዘሪ ዘሩን ሊዘራ ወጣ። ሲዘራም አንዳንዱ በመንገድ ዳር ወደቀ ተረገጠም፣ የሰማይ ወፎችም በሉት። ሌላውም በዓለት ላይ ወደቀ፣ በበቀለም ጊዜ እርጥበት ስላልነበረው ደረቀ። ሌላውም በእሾህ መካከል ወደቀ፣ እሾሁም አብሮ በቀለና አነቀው። ሌላውም በመልካም መሬት ላይ ወደቀ፤ በበቀለም ጊዜ መቶ እጥፍ አፈራ።”—ሉቃስ 8:5-8
-
-
የአምላክን ቃል መውደድ የሚያስገኛቸው ጥቅሞችመጠበቂያ ግንብ—1999 | ኅዳር 1
-
-
9. (ሀ) በመንገድ ዳር (ለ) በአለት ላይ (ሐ) በእሾሀማ መሬት ላይ የሚወድቀው ዘር ምን ያመለክታል?
9 ኢየሱስ አንዳንዱ ዘር በመንገድ ዳር እንደሚወድቅና እንደሚረጋገጥ ገልጿል። ይህም የመንግሥቱ ዘር በልባቸው ውስጥ ሥር እንዳይሰድ በብዙ ነገር የተጠላለፉ ሰዎችን ያመለክታል። ለአምላክ ቃል ፍቅር ከማዳበራቸው በፊት “ዲያብሎስ ይመጣል አምነውም እንዳይድኑ ቃሉን ከልባቸው ይወስዳል።” (ሉቃስ 8:12) አንዳንዱ ዘር ደግሞ አለት ላይ ይወድቃል። ይህ ደግሞ የመጽሐፍ ቅዱስን መልእክት ደስ ብሏቸው የሚቀበሉትንና ነገር ግን ቃሉ ልባቸውን እንዲነካ የማይፈቅዱለትን ሰዎች ያመለክታል። ተቃውሞ ሲገጥማቸው ወይም የመጽሐፍ ቅዱስን ምክር ሥራ ላይ ማዋሉ ከባድ እንደሆነ ሲሰማቸው ሥር ስለሌላቸው ‘ይክዳሉ።’ (ሉቃስ 8:13) ከዚያ ደግሞ ቃሉን የሚሰሙ ነገር ግን በዚህ ሕይወት ‘አሳብና የባለ ጠግነት ምቾት’ የሚዋጡ ሰዎች አሉ። በመጨረሻም በእሾህ እንደተያዘ ተክል ሙሉ በሙሉ “ይታነቃሉ።”—ሉቃስ 8:14
-