-
ኢየሱስ በመንግሥቱ ክብር ሲመጣመጠበቂያ ግንብ—1997 | ግንቦት 15
-
-
4 ሦስቱ ሐዋርያት የተመለከቱት ነገር ምን ነበር? ሉቃስ ሁኔታውን በተመለከተ የሚከተለውን መግለጫ ሰጥቷል:- “[ኢየሱስ] ሲጸልይም የፊቱ መልክ ተለወጠ፤ ልብሱም ተብለጭልጮ ነጭ ሆነ። እነሆም፣ ሁለት ሰዎች እነርሱም ሙሴና ኤልያስ ከእርሱ ጋር ይነጋገሩ ነበር፤ በክብርም ታይተው በኢየሩሳሌም ሊፈጸም ስላለው ስለ መውጣቱ ይናገሩ ነበር።” ከዚያም “ደመና መጣና [ሐዋርያቱን] ጋረዳቸው፤ ወደ ደመናውም ሲገቡ ሳሉ ፈሩ። ከደመናውም:- የመረጥሁት ልጄ ይህ ነው፣ እርሱን ስሙት የሚል ድምፅ መጣ።”— ሉቃስ 9:29-31, 34, 35
-
-
ኢየሱስ በመንግሥቱ ክብር ሲመጣመጠበቂያ ግንብ—1997 | ግንቦት 15
-
-
5. ኢየሱስ በተአምራዊ ሁኔታ መለወጡ በሐዋርያው ጴጥሮስ ላይ ምን ውጤት አስከትሏል?
5 ሐዋርያው ጴጥሮስ ቀደም ብሎ ኢየሱስን “ክርስቶስ የሕያው እግዚአብሔር ልጅ” ሲል ጠርቶታል። (ማቴዎስ 16:16) ይሖዋ ከሰማይ የተናገራቸው ቃላት የዚህን አባባል ትክክለኛነት ያረጋገጡ ሲሆን ኢየሱስ በተአምራዊ ሁኔታ ሲለወጥ የታየበት ራእይ ደግሞ ክርስቶስ በመንግሥታዊ ሥልጣንና ክብር እንደሚመጣና በመጨረሻም በሰው ልጆች ላይ እንደሚፈርድ የሚያመለክት ነበር። ኢየሱስ በተአምራዊ ሁኔታ ከተለወጠ 30 ከሚበልጡ ዓመታት በኋላ ጴጥሮስ እንዲህ ሲል ጽፏል:- “የእርሱን ግርማ አይተን እንጂ በብልሃት የተፈጠረውን ተረት ሳንከተል የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ኃይልና መምጣት አስታወቅናችሁ። ከገናናው ክብር:- በእርሱ ደስ የሚለኝ ልጄ ይህ ነው የሚል ያ ድምፅ በመጣለት ጊዜ ከእግዚአብሔር አብ ክብርንና ምስጋናን ተቀብሎአልና፤ እኛም በቅዱሱ ተራራ ከእርሱ ጋር ሳለን ይህን ድምፅ ከሰማይ ሲወርድ ሰማን።”— 2 ጴጥሮስ 1:16-18፤ 1 ጴጥሮስ 4:17
-