-
ኢየሱስ 70 ደቀ መዛሙርት ላከመጠበቂያ ግንብ—1998 | መጋቢት 1
-
-
ኢየሱስ ለደቀ መዛሙርቱ ተጨማሪ መመሪያ ሲሰጥ “ኮረጆም ከረጢትም ጫማም አትያዙ፤ በመንገድም ለማንም እጅ አትንሡ” ብሏቸዋል። (ሉቃስ 10:4) አንድ መንገደኛ ከረጢትና ምግብ ብቻ ሳይሆን የጫማው ሶል ሊያልቅና ማሰሪያውም ሊበጠስ ስለሚችል አንድ ትርፍ ጫማም መያዙ የተለመደ ነበር። ሆኖም የኢየሱስ ደቀ መዛሙርት ለእነዚህ ዓይነት ነገሮች መጨነቅ አልነበረባቸውም። ከዚህ ይልቅ ይሖዋ የእንግዳ ተቀባይነት ባሕል ባላቸው መሰል እስራኤላውያን ተጠቅሞ እንደሚንከባከባቸው ማመን ነበረባቸው።
ታዲያ ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱ ሰላምታ ለመስጠት ማንንም ማቀፍ እንደሌለባቸው የነገራቸው ለምንድን ነው? የወዳጅነት መንፈስ የሌላቸው እንዲያውም ክፉ መሆን ሊኖርባቸው ነውን? በጭራሽ! ሰላምታ ለመስጠት ማቀፍ የሚል ትርጉም ያለው ኤስፓዞማይ የሚለው የግሪክኛ ቃል አክብሮት ባለው መንገድ “እንደምን አደርክ” ወይም “እንደምን ዋልክ” ከማለት የበለጠ ሊሆን ይችላል። ባሕላዊ የሆነውን መሳሳም፣ መተቃቀፍና ሁለት ጓደኛሞች ሲገናኙ የሚከተለውን ረዥም ጭውውት ሊያጠቃልልም ይችላል። አንድ ተንታኝ ስለዚህ ሲገልጹ “በሩቅ ምሥራቅ የሚኖሩ ሰዎች ሰላምታ የሚለዋወጡት እኛ እንደምናደርገው በትንሹ አንገት ሰበር በማድረግ ወይም በመጨባበጥ ሳይሆን ደጋግሞ በመተቃቀፍና በመስገድ እንዲሁም መሬት ላይ በመደፋት ጭምር የሚደረግ ነበር። ይህ ሁሉ ረዥም ጊዜ የሚጠይቅ ነበር” ብለዋል። (ከ2 ነገሥት 4:29 ጋር አወዳድር።) በመሆኑም እነዚህ ድርጊቶች ምንም እንኳ ባሕላዊ ቢሆኑም አላስፈላጊ የሆኑ ትኩረት የሚከፋፍሉ ነገሮችን እንዲያስወግዱ ኢየሱስ ተከታዮቹን ረድቷቸዋል።
-
-
ኢየሱስ 70 ደቀ መዛሙርት ላከመጠበቂያ ግንብ—1998 | መጋቢት 1
-
-
በአሁኑ ጊዜ የአምላክን መንግሥት ምስራች የመስበክና ደቀ መዛሙርት የማፍራት ተልዕኮው ከ5,000,000 በሚበልጡ የይሖዋ ምሥክሮች በዓለም ዙሪያ እየተሠራ ነው። (ማቴዎስ 24:14፤ 28:19, 20) የሚያሰራጩት መልእክት አጣዳፊ መሆኑን ተገንዝበዋል። ስለዚህ ጊዜያቸውን በአግባቡ ይጠቀሙበታል። በጣም አስፈላጊ ለሆነው ሥራቸው ሙሉ ትኩረት እንዳይሰጡ የሚከለክሏቸውን ማዘናጊያዎች ያስወግዳሉ።
የይሖዋ ምሥክሮች ለሚያገኟቸው ሰዎች ሁሉ ልባዊ ስሜት ለማሳየት ይጥራሉ። የሆነ ሆኖ በማያስፈልግ ወሬ ራሳቸውን አያስጠምዱም፣ ማኅበራዊ በሆኑ ጉዳዮች ላይ በመከራከር ወይም ዓለም ፍትሕ ለማስፈን በሚያደርገው ከንቱ ጥረት ራሳቸውን አያስገቡም። (ዮሐንስ 17:16) ከዚህ ይልቅ ውይይታቸው የሚያተኩረው ለዘለቄታው የሰው ልጆችን ችግር በሚያስወግደው ብቸኛው የአምላክ መንግሥት ላይ ነው።
-