-
ይሖዋ “ለሚለምኑት መንፈስ ቅዱስ” ይሰጣቸዋልመጠበቂያ ግንብ—2006 | ታኅሣሥ 15
-
-
5. ወዳጁን ስለነዘነዘው ሰው የሚገልጸው ምሳሌ ስንጸልይ ሊኖረን የሚገባውን አመለካከት አስመልክቶ ምን ያስተምረናል?
5 የሚፈልገውን ነገር ሳይታክት ስለጠየቀው ሰው የሚናገረው ይህ ሕያው ምሳሌ፣ በምንጸልይበት ጊዜ ምን አመለካከት ሊኖረን እንደሚገባ በግልጽ ያሳያል። ኢየሱስ ሰውየው የሚፈልገውን ነገር ያገኘው “ስለ ንዝነዛው” መሆኑን ተናግሯል። (ሉቃስ 11:8) ‘መነዝነዝ’ የሚለው ቃል በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የተጠቀሰው አንድ ጊዜ ብቻ ነው። መነዝነዝ ተብሎ የተተረጎመው ግሪክኛ ቃል ቀጥተኛ ፍቺው “እፍረተቢስ” የሚል ነው። እፍረተቢስ የሚለው ቃል ብዙውን ጊዜ መጥፎ ባሕርይን ያመለክታል። ይሁንና አንድ ሰው እፍረተቢስ የሚሆነው ወይም የሚነዘንዘው መልካም ነገሮችን ለማግኘት ብሎ ከሆነ ይህ የሚያስመሰግነው ባሕርይ ነው ሊባል ይችላል። ይህ ሁኔታ እንግዳ በመጣበት ሰውዬ ላይ ታይቷል። ሰውየው አፍሮ የሚፈልገውን ነገር ከመጠየቅ ወደኋላ አላለም። ኢየሱስ ይህን ሰው ምሳሌ አድርጎ ስላቀረበልን እኛም ሳንታክት መጸለይ ይኖርብናል። ይሖዋ ‘ሳናቋርጥ እንድንለምን፣ ሳናቋርጥ እንድንፈልግና ሳናቋርጥ እንድናንኳኳ’ ይሻል። በምላሹም ይሖዋ ‘ለሚለምኑት መንፈስ ቅዱስን አብልጦ ይሰጣቸዋል።’
-
-
ይሖዋ “ለሚለምኑት መንፈስ ቅዱስ” ይሰጣቸዋልመጠበቂያ ግንብ—2006 | ታኅሣሥ 15
-
-
9, 10. (ሀ) አምላክ ቅዱስ መንፈሱን እንዲሰጠን በተደጋጋሚ መለመናችን አስፈላጊ የሆነው ለምን እንደሆነ በምሳሌ አስረዳ። (ለ) ራሳችንን ምን ብለን መጠየቅ ይኖርብናል? ለምንስ?
9 በዛሬው ጊዜ ይህን ትምህርት በሥራ ላይ ለማዋል እንድንችል እንዲረዳን አንድ ምሳሌ እንመልከት። ከቤተሰብህ አባላት ውስጥ አንዱ በእኩለ ሌሊት ታመመ እንበል። እርዳታ ለማግኘት አንድን ሐኪም ከእንቅልፉ ትቀሰቅሰዋለህ? ቀላል ሕመም ከሆነ እንዲህ ላታደርግ ትችላለህ። ይሁንና በሽታው ልብ ድካም ቢሆን ሐኪሙን ለመጥራት ይሉኝታ አይዝህም። ለምን? አጣዳፊ ሁኔታ ስለገጠመህ ነው። የባለሙያ እርዳታ የግድ እንደሚያስፈልግህ ተገንዝበሃል። እርዳታ አለመጠየቅህ በሽተኛውን ለሞት ሊዳርገው ይችላል። በተመሳሳይም እውነተኛ ክርስቲያኖች ቀጣይ የሆነ አንድ ዓይነት አጣዳፊ ጉዳይ አጋጥሟቸዋል ለማለት ይቻላል። ደግሞም ሰይጣን እኛን ለመዋጥ ልክ “እንደሚያገሣ አንበሳ” በመዞር ላይ ነው። (1 ጴጥሮስ 5:8) በመንፈሳዊ ሕያው ሆነን ለመቀጠል የአምላክ መንፈስን እርዳታ ማግኘታችን የግድ አስፈላጊ ነው። የአምላክን እርዳታ አለመጠየቅ አስከፊ ጉዳት ሊያስከትልብን ይችላል። በመሆኑም አምላክ ቅዱስ መንፈሱን እንዲሰጠን ሳንታክት እንለምናለን። (ኤፌሶን 3:14-16) ‘እስከ መጨረሻው ለመጽናት’ የሚረዳንን ጥንካሬ ማግኘት የምንችለው እንዲህ ስናደርግ ብቻ ነው።—ማቴዎስ 10:22፤ 24:13
-