-
ይሖዋ “ለሚለምኑት መንፈስ ቅዱስ” ይሰጣቸዋልመጠበቂያ ግንብ—2006 | ታኅሣሥ 15
-
-
11. ኢየሱስ ስለ አባትና ልጅ የሚናገረውን ምሳሌ ከጸሎት ጋር ያያዘው እንዴት ነው?
11 ኢየሱስ እንግዳ ስለመጣበት ሰው የተናገረው ምሳሌ አንድ አማኝ ጸሎት ሲያቀርብ ሊኖረው የሚገባውን ዝንባሌ አጉልቶ ይገልጻል። ቀጣዩ ምሳሌ ደግሞ የጸሎት ሰሚውን ማለትም የይሖዋ አምላክን ስሜት የሚያጎላ ነው። ኢየሱስ “ከእናንተ መካከል አባት ሆኖ ሳለ ልጁ ዓሣ ቢለምነው እባብ የሚሰጠው ይኖራልን? ወይስ ዕንቊላል ቢለምነው ጊንጥ ይሰጠዋልን?” የሚል ጥያቄ አቅርቧል። ከዚያም ኢየሱስ ምሳሌው ከጸሎት ጋር እንዴት እንደሚያያዝ ሲገልጽ “እናንተ ክፉዎች ሆናችሁ ሳላችሁ፣ ለልጆቻችሁ መልካም ስጦታን መስጠት ካወቃችሁበት፣ የሰማዩ አባታችሁ ታዲያ ለሚለምኑት መንፈስ ቅዱስን እንዴት አብልጦ አይሰጥ!” ብሏል።—ሉቃስ 11:11-13
12. ልጁ የሚለምነውን ነገር ስለሚሰጥ አባት የሚናገረው ምሳሌ ይሖዋ ለጸሎታችን ምላሽ ለመስጠት ፈቃደኛ መሆኑን የሚያጎላው እንዴት ነው?
12 ኢየሱስ፣ ለልጁ ምላሽ ስለሚሰጥ አባት በተናገረው ምሳሌ ላይ ይሖዋ በጸሎት ወደ እርሱ ስለሚቀርቡ ሰዎች ያለውን ስሜት ገልጿል። (ሉቃስ 10:22) በመጀመሪያ ደረጃ፣ በቀረቡት ሁለት ምሳሌዎች መካከል ያለውን ልዩነት ልብ በል። ይሖዋ፣ በመጀመሪያው ምሳሌ ላይ እንደተጠቀሰው ሰው እርዳታ ሲጠየቅ ምላሽ ለመስጠት የሚያቅማማ አምላክ ሳይሆን ለልጁ ጥያቄ አፋጣኝ ምላሽ እንደሚሰጥ አፍቃሪ ሰብዓዊ ወላጅ ነው። (መዝሙር 50:15) ከዚህም በተጨማሪ በሰማይ የሚኖረውን አባት ከአንድ ሰብዓዊ አባት ጋር በማወዳደር ይሖዋ እኛን ለመርዳት ፈቃደኛ መሆኑን ጠቅሷል። ኢየሱስ አንድ ሰብዓዊ አባት በወረሰው ኃጢአት ምክንያት “ክፉ” ቢሆንም እንኳ ለልጁ መልካም ስጦታ የሚሰጥ ከሆነ ለጋስ የሆነው የሰማዩ አባታችን እንደ ቤተሰቡ ለሚያያቸው አምላኪዎቹ መንፈስ ቅዱስን አብልጦ እንደሚሰጥ መጠበቃችን ምንኛ ተገቢ ነው!—ያዕቆብ 1:17
-
-
ይሖዋ “ለሚለምኑት መንፈስ ቅዱስ” ይሰጣቸዋልመጠበቂያ ግንብ—2006 | ታኅሣሥ 15
-
-
14. (ሀ) መከራ የደረሰባቸው አንዳንድ ሰዎች የትኛው የተሳሳተ ሐሳብ ያጠቃቸዋል? (ለ) መከራዎች ሲደርሱብን ተማምነን ወደ ይሖዋ መጸለይ ያለብን ለምንድን ነው?
14 ከዚህ ባሻገር ኢየሱስ ስለ አፍቃሪ አባት የተናገረው ምሳሌ የይሖዋ ጥሩነት ማንኛውም ሰብዓዊ ወላጅ ከሚያሳየው ቸርነት እጅግ የላቀ መሆኑን አጉልቶ ያሳያል። ከዚህም የተነሳ ማናችንም ብንሆን ችግሮች ሲገጥሙን ይህ የሆነው አምላክ ስላዘነብን ነው ብለን ፈጽሞ ማሰብ አይገባንም። እንዲህ እንድናስብ የሚፈልገው ቀንደኛው ጠላታችን ሰይጣን ነው። (ኢዮብ 4:1, 7, 8፤ ዮሐንስ 8:44) አንድ ሰው ራሱን እንዲኮንን የሚያበረታታ ቅዱስ ጽሑፋዊ ሐሳብ የለም። ይሖዋ “በክፉ” አይፈትነንም። (ያዕቆብ 1:13) እንዲሁም እባብ መሰል መከራ ወይም ጊንጥ የሚመስል ፈተና አያደርስብንም። የሰማዩ አባታችን “ለሚለምኑት መልካም ስጦታን” ይሰጣቸዋል። (ማቴዎስ 7:11፤ ሉቃስ 11:13) ስለ ይሖዋ ጥሩነትና እኛን ለመርዳት ስላለው የፈቃደኝነት መንፈስ በተገነዘብን መጠን ተማምነን ወደ እርሱ ለመጸለይ ይበልጥ እንገፋፋለን። እንዲህ ባደረግን ቁጥር እኛም “እግዚአብሔር በእርግጥ ሰምቶኛል፤ ጸሎቴንም አድምጦአል” ሲል እንደጻፈው መዝሙራዊ ለማለት እንነሳሳለን።—መዝሙር 10:17፤ 66:19
-