-
የመጽሐፍ ቅዱስ መጽሐፍ ቁጥር 39—ሚልክያስ“ቅዱሳት መጻሕፍት ሁሉ” ትክክለኛና ጠቃሚ ናቸው፣ ጥራዝ 15
-
-
4 የሚልክያስን መጽሐፍ ትክክለኛነት በተመለከተ በአይሁዳውያን ዘንድ ጥያቄ ተነስቶ አያውቅም። በክርስቲያን ግሪክኛ ቅዱሳን መጻሕፍት ውስጥ ከሚልክያስ መጽሐፍ ላይ የተወሰዱ ጥቅሶች የሚገኙ ሲሆን ከእነዚህም መካከል የትንቢቱን ፍጻሜ የሚያሳዩ በርካታ ሐሳቦች እናገኛለን። ይህም የሚልክያስ መጽሐፍ በአምላክ መንፈስ አነሳሽነት እንደተጻፈና በክርስቲያን ጉባኤ ዘንድ ተቀባይነት ያገኙት የዕብራይስጥ ቅዱሳን መጻሕፍት ክፍል እንደሆነ ያረጋግጣል።—ሚል. 1:2, 3—ሮሜ 9:13፤ ሚል. 3:1—ማቴ. 11:10 እንዲሁም ሉቃስ 1:76 እና 7:27፤ ሚል. 4:5, 6—ማቴ. 11:14 እና 17:10-13 እንዲሁም ማር. 9:11-13 እና ሉቃስ 1:17
-
-
የመጽሐፍ ቅዱስ መጽሐፍ ቁጥር 39—ሚልክያስ“ቅዱሳት መጻሕፍት ሁሉ” ትክክለኛና ጠቃሚ ናቸው፣ ጥራዝ 15
-
-
14 ሚልክያስ በመንፈስ አነሳሽነት የተጻፉት የዕብራይስጥ ቅዱሳን መጻሕፍት የመጨረሻ ክፍል እንደመሆኑ መጠን በመሲሑ መምጣት ዙሪያ ያሉትን ሁኔታዎች አስቀድሞ ጠቁሟል፤ ከአራት መቶ ዘመናት በኋላ መሲሑ መምጣቱ ደግሞ ለክርስቲያን ግሪክኛ ቅዱሳን መጻሕፍት መጻፍ ምክንያት ሆኗል። በሚልክያስ 3:1 ላይ ተመዝግቦ እንደሚገኘው የሠራዊት ጌታ ይሖዋ “እነሆ፤ በፊቴ መንገድ እንዲያዘጋጅ መልእክተኛዬን እልካለሁ” ሲል ተናግሯል። በዕድሜ የገፋው ዘካርያስ እነዚህ ቃላት በልጁ በመጥምቁ ዮሐንስ ላይ ፍጻሜያቸውን እንዳገኙ በአምላክ መንፈስ ተነሳስቶ ተናግሯል። (ሉቃስ 1:76) ኢየሱስም እንደሚከተለው ብሎ በተናገረ ጊዜ የዚህን ሐሳብ ትክክለኛነት አረጋግጧል:- “እንደ መጥምቁ ዮሐንስ ያለ አልተነሣም፤ ሆኖም በመንግሥተ ሰማያት ከሁሉ የሚያንሰው ይበልጠዋል።” ሚልክያስ አስቀድሞ እንደተናገረው ዮሐንስ የተላከው ‘መንገድ ለማዘጋጀት’ በመሆኑ ከጊዜ በኋላ ከኢየሱስ ጋር የመንግሥት ቃል ኪዳን ከገቡት ሰዎች መካከል አልነበረም።—ማቴ. 11:7-12፤ ሉቃስ 7:27, 28፤ 22:28-30
-