የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • ‘በአምላክ ዘንድ ሀብታም’ ነህ?
    መጠበቂያ ግንብ—2007 | ነሐሴ 1
    • 7. በኢየሱስ ምሳሌ ላይ ያለው ሰው ያጋጠመውን ችግር የፈታው እንዴት ነበር?

      7 ኢየሱስ ወደተናገረው ምሳሌ ስንመለስ፣ ሀብታሙ ሰው ምርቱን የሚያስቀምጥበት ቦታ እስኪያጣ ድረስ እርሻው ፍሬያማ በሆነለት ጊዜ ምን አደረገ? ያሉትን ጎተራዎች አፍርሶ የተትረፈረፈ ምርቱንና ንብረቱን የሚያስቀምጥባቸው ትልልቅ ጎተራዎች ለመሥራት ወሰነ። ያወጣው ዕቅድ እንዲረካና ሕይወቱ አስተማማኝ እንደሆነ እንዲሰማው ሳያደርገው አልቀረም፤ በዚህም የተነሳ እንዲህ ብሎ አሰበ:- “ነፍሴንም፣ ‘ነፍሴ ሆይ፤ ለብዙ ዘመን የሚበቃሽ ሀብት አከማችቼልሻለሁ፤ እንግዲህ ዕረፊ፤ ብዪ፤ ጠጪ፤ ደስም ይበልሽ’ እላታለሁ።”—ሉቃስ 12:19

      “ሞኝ” የተባለው ለምንድን ነው?

      8. በኢየሱስ ምሳሌ ላይ የተጠቀሰው ሰው የዘነጋው አስፈላጊ ነገር ምን ነበር?

      8 ከኢየሱስ አነጋገር መመልከት እንደሚቻለው ግን የሀብታሙ ሰው ዕቅድ አስተማማኝ አልነበረም። ዕቅዱ ጥሩ ቢመስልም በጣም አስፈላጊ የሆነውን ነገር ይኸውም የአምላክን ፈቃድ ከግምት ያስገባ አልነበረም። ሰውየው ያሰበው ስለራሱ ብቻ ነበር፤ ለማረፍ፣ ለመብላት፣ ለመጠጣትና ለመደሰት እንደሚችል አስቦ ነበር። ብዙ “ሀብት” ስላለው “ለብዙ ዘመን” መኖር እንደሚችልም ተሰምቶት ነበር። የሚያሳዝነው ግን ነገሮች እንዳሰበው አልሆኑለትም። ኢየሱስ አስቀድሞ እንደተናገረው:- “የሰው ሕይወቱ በሀብቱ ብዛት የተመሠረተ [አይደለም]።” (ሉቃስ 12:15) የዚያኑ ዕለት ሌሊት አምላክ ይህን ሰው “አንተ ሞኝ፤ ነፍስህን በዚህች ሌሊት ከአንተ ሊወስዱ ይፈልጓታል፤ እንግዲህ፣ ለራስህ ያከማቸኸው ለማን ይሆናል?” አለው፤ በመሆኑም ሰውየው የለፋበት ነገር ሁሉ በድንገት ከንቱ ሆነ።—ሉቃስ 12:20

  • ‘በአምላክ ዘንድ ሀብታም’ ነህ?
    መጠበቂያ ግንብ—2007 | ነሐሴ 1
    • 10. አንድ ሰው ብዙ “ሀብት” ያለው መሆኑ “ለብዙ ዘመን” እንደሚኖር ዋስትና የማይሆነው ለምንድን ነው?

      10 እኛም በዚህ ትምህርት ላይ ማሰላሰላችን ጠቃሚ ነው። በምሳሌው ላይ እንደተጠቀሰው ሰው፣ ብዙ “ሀብት” ለማካበት ተግተን በመሥራት ተጠምደን “ለብዙ ዘመን” መኖር እንድንችል ማድረግ ያለብንን ነገር ሳናደርግ እንቀር ይሆን? (ዮሐንስ 3:16፤ 17:3) መጽሐፍ ቅዱስ “በቍጣ ቀን ሀብት ፋይዳ የለውም” እንዲሁም “በሀብቱ የሚታመን ሁሉ ይወድቃል” ይላል። (ምሳሌ 11:4, 28) በመሆኑም ኢየሱስ “ለራሱ ሀብት የሚያከማች፣ ዳሩ ግን በእግዚአብሔር ዘንድ ሀብታም ያልሆነ ሰው መጨረሻው ይኸው ነው” በሚለው ምክር ምሳሌውን ደምድሟል።—ሉቃስ 12:21

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ