-
“ይሖዋ፣ መሐሪና ሞገስ ያለው አምላክ”መጠበቂያ ግንብ—1998 | ጥቅምት 1
-
-
12, 13. በዛሬው ጊዜ አንዳንዶች ወደ ልባቸው እንዲመለሱ የረዳቸው ምንድን ነው? (ሣጥኑን ተመልከት።)
12 “ወደ ልቡም ተመልሶ እንዲህ አለ:- እንጀራ የሚተርፋቸው የአባቴ ሞያተኞች ስንት ናቸው? እኔ ግን ከዚህ በራብ እጠፋለሁ። ተነሥቼም ወደ አባቴ እሄዳለሁና:- አባቴ ሆይ፣ በሰማይና በፊትህ በደልሁ፣ ወደ ፊትም ልጅህ ልባል አይገባኝም፤ ከሞያተኞችህ እንደ አንዱ አድርገኝ እለዋለሁ። ተነሥቶም ወደ አባቱ መጣ።”—ሉቃስ 15:17-20
-
-
“ይሖዋ፣ መሐሪና ሞገስ ያለው አምላክ”መጠበቂያ ግንብ—1998 | ጥቅምት 1
-
-
14. አባካኙ ልጅ ምን ለማድረግ ወሰነ? ይህን በማድረጉስ ትሕትና ያሳየው እንዴት ነበር?
14 ሆኖም ከእውነት መንገድ ወጥተው የባዘኑ ሰዎች ምን ማድረግ ይችላሉ? በኢየሱስ ምሳሌ ላይ የተጠቀሰው ኮብላይ ልጅ ወደ ቤቱ ተመልሶ ለመሄድና አባቱን ይቅርታ ለመለመን ወስኗል። “ከሞያተኞችህ እንደ አንዱ አድርገኝ” ብሎ ለመጠየቅ ቆረጠ። አንድ ሞያተኛ በተፈለገው ጊዜ ሊባረር የሚችል የቀን ሠራተኛ ነበር። ይህ ደግሞ ከሞላ ጎደል እንደ አንድ የቤተሰብ አባል ተደርጎ ይቆጠር ከነበረ ባሪያ ያነሰ ደረጃ ያለው ነበር። ስለዚህ አባካኙ ልጅ ቀደም ሲል ወደነበረው የልጅነት ቦታ እንዲመለስ የመጠየቅ ሐሳብ አልነበረውም። ከቀን ወደ ቀን ለአባቱ ያለውን ታማኝነት እንደ አዲስ ለማስመስከር ሲል የመጨረሻውን አነስተኛ ቦታ ለመቀበል ፈቃደኛ ነበር። ይሁን እንጂ አባካኙ ልጅ ያላሰበው ነገር ጠበቀው።
-