-
“ይሖዋ፣ መሐሪና ሞገስ ያለው አምላክ”መጠበቂያ ግንብ—1998 | ጥቅምት 1
-
-
15–17. (ሀ) አባትየው ልጁን በተመለከተ ጊዜ ምን አደረገ? (ለ) አባትየው ለልጁ የሰጠው ልብስ፣ ቀለበትና ጫማ ምን ያመለክታሉ? (ሐ) አባትየው ግብዣ ማዘጋጀቱ ምን ያሳያል?
15 “እርሱም ገና ሩቅ ሳለ አባቱ አየውና አዘነለት፣ ሮጦም አንገቱን አቀፈውና ሳመው። ልጁም:- አባቴ ሆይ፣ በሰማይና በፊትህ በደልሁ፣ ወደ ፊትም ልጅህ ልባል አይገባኝም [“ከሞያተኞችህ እንደ አንዱ አድርገኝ፣” NW] አለው። አባቱ ግን ባሪያዎቹን አለ:- ፈጥናችሁ ከሁሉ የተሻለ ልብስ አምጡና አልብሱት፣ ለእጁ ቀለበት ለእግሩም ጫማ ስጡ፤ የሰባውን ፊሪዳ አምጥታችሁ እረዱት፣ እንብላም ደስም ይበለን፤ ይህ ልጄ ሞቶ ነበርና ደግሞም ሕያው ሆኖአል፤ ጠፍቶም ነበር ተገኝቶአልም። ደስም ይላቸው ጀመር።”—ሉቃስ 15:20–24
-
-
“ይሖዋ፣ መሐሪና ሞገስ ያለው አምላክ”መጠበቂያ ግንብ—1998 | ጥቅምት 1
-
-
17 አባትየው ልጁ ጋ ሲደርስ አንገቱን እቅፍ አድርጎ ሳመው። ከዚያም ልብስ፣ ቀለበትና ጫማ እንዲሰጡት ባሪያዎቹን አዘዘ። ልብሱ እንዲሁ ተራ ልብስ ሳይሆን “ከሁሉ የተሻለ” ምናልባትም ለተከበረ እንግዳ የሚቀርብ በጌጣ ጌጥ የተንቆጠቆጠ ልብስ ሳይሆን አይቀርም። አብዛኛውን ጊዜ ባሪያዎች ቀለበትና ጫማ አድርገው ስለማይታዩ አባትየው ልጁ እንደገና የቤተሰቡ አባል በመሆን ሙሉ በሙሉ ተቀባይነት ማግኘቱን ግልጽ ማድረጉ ነበር። ሆኖም አባትየው ሌላም ነገር አድርጓል። የልጁን መመለስ ለማክበር ግብዣ እንዲዘጋጅ አዘዘ። በግልጽ ለማየት እንደሚቻለው ይህ ሰው ልጁን ይቅርታ ያደረገለት ቅር እያለው ወይም የልጁ መመለስ ስላስገደደው አልነበረም፤ ይቅርታ ሊያደርግለት ፈልጎ ነበር። የልጁ መመለስ ከልብ አስደስቶት ነበር።
-