-
እውነተኛ የሆነውን ሀብት መፈለግመጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2017 | ሐምሌ
-
-
4, 5. (ሀ) ኢየሱስ በተናገረው ምሳሌ ላይ የተጠቀሰው መጋቢ ምን አጋጥሞት ነበር? (ለ) ኢየሱስ ለተከታዮቹ ምን ምክር ሰጥቷቸዋል?
4 ሉቃስ 16:1-9ን አንብብ። ኢየሱስ ስለ ዓመፀኛው መጋቢ የተናገረው ምሳሌ ትኩረት የሚስብ ነው። ይህ መጋቢ፣ የጌታውን ንብረት እያባከነ ነው ተብሎ እንደተከሰሰ ሰማ፤ በመሆኑም የመጋቢነት ሥራውን ሲያጣ የሚረዱት “ወዳጆች” ለማፍራት ሲል ‘አርቆ አሳቢነት’ የሚንጸባረቅበት እርምጃ ወስዷል።a ኢየሱስ ይህን ምሳሌ የተናገረው፣ ተከታዮቹ በዚህ ዓለም ውስጥ ለመኖር ሲሉ ታማኝነት የጎደለው ድርጊት እንዲፈጽሙ ለማበረታታት እንዳልሆነ ግልጽ ነው። መጋቢው የወሰደው እርምጃ “የዚህ ሥርዓት ልጆች” የሚያደርጉት ነገር እንደሆነ ኢየሱስ ገልጿል፤ ሆኖም ይህን ምሳሌ አንድ ትምህርት ለማስተላለፍ ተጠቅሞበታል።
5 ኢየሱስ፣ አስቸጋሪ ሁኔታ እንዳጋጠመው መጋቢ ሁሉ አብዛኞቹ ተከታዮቹም ፍትሕ የጎደለው የንግድ ሥርዓት ባለበት በዚህ ዘመን መተዳደሪያ ማግኘት ከባድ ሊሆንባቸው እንደሚችል ያውቃል። በመሆኑም እንደሚከተለው በማለት አሳስቧቸዋል፦ “በዓመፅ ሀብት ለራሳችሁ ወዳጆች አፍሩ፤ እነሱም [ይሖዋና ኢየሱስ] የዓመፅ ሀብት ሲያልቅ በዘላለማዊ መኖሪያ ይቀበሏችኋል።” ኢየሱስ ከሰጠው ምክር ምን ትምህርት እናገኛለን?
6. በዛሬው ጊዜ ያለው የንግድ ሥርዓት በአምላክ ዓላማ ውስጥ እንዳልነበረ እንዴት ማወቅ እንችላለን?
6 ኢየሱስ ቁሳዊ ነገሮችን “የዓመፅ ሀብት” ብሎ የጠራቸው ለምን እንደሆነ ባይናገርም፣ ስግብግብነት የሚንጸባረቅበት የንግድ ሥርዓት በአምላክ ዓላማ ውስጥ እንዳልነበረ መጽሐፍ ቅዱስ በግልጽ ያሳያል። ይሖዋ፣ አዳምና ሔዋን በኤደን እያሉ የሚያስፈልጋቸውን ነገር ሁሉ አትረፍርፎ ሰጥቷቸዋል። (ዘፍ. 2:15, 16) ከጊዜ በኋላ ደግሞ፣ አምላክ በመጀመሪያው መቶ ዘመን ለነበሩት ቅቡዓን ክርስቲያኖች ቅዱስ መንፈሱን ከሰጣቸው በኋላ የነበረውን ሁኔታ መጽሐፍ ቅዱስ ሲገልጽ እንዲህ ይላል፦ “አንዳቸውም ቢሆኑ ያላቸው ማንኛውም ንብረት የግላቸው እንደሆነ አድርገው አይቆጥሩም ነበር፤ ከዚህ ይልቅ ያላቸው ነገር ሁሉ የጋራ ነበር።” (ሥራ 4:32) ነቢዩ ኢሳይያስም የሰው ልጆች በሙሉ የምድርን ሀብት በነፃ መጠቀም የሚችሉበት ጊዜ እንደሚመጣ ተንብዮአል። (ኢሳ. 25:6-9፤ 65:21, 22) እስከዚያው ድረስ ግን የኢየሱስ ተከታዮች በዛሬው ጊዜ ያለውን “የዓመፅ ሀብት” በመጠቀም መተዳደሪያ ለማግኘት፣ ‘አርቀው ማሰብ’ ወይም “ብልሆች” መሆን ያስፈልጋቸዋል፤ በእርግጥ ይህን ሲያደርጉ አምላክን ማስደሰት እንዳለባቸውም አይዘነጉም።
-
-
እውነተኛ የሆነውን ሀብት መፈለግመጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2017 | ሐምሌ
-
-
7. በሉቃስ 16:10-13 ላይ ምን ምክር ተሰጥቶናል?
7 ሉቃስ 16:10-13ን አንብብ። ኢየሱስ በተናገረው ምሳሌ ላይ የተጠቀሰው መጋቢ ወዳጆችን ያፈራው ለግል ጥቅሙ ሲል ነው። ኢየሱስ በሰማይ ወዳጆች እንዲያፈሩ ተከታዮቹን ሲያሳስባቸው ግን ይህን በራስ ወዳድነት ተነሳስተው እንዲያደርጉት ማበረታታቱ አልነበረም። ኢየሱስ ከተናገረው ምሳሌ ቀጥሎ ባሉት ቁጥሮች ላይ፣ “በዓመፅ ሀብት” መጠቀም ለአምላክ ታማኝ ከመሆን ጋር ተያይዞ ተገልጿል። ኢየሱስ ሊያጎላ የፈለገው ነጥብ፣ ያለንን የዓመፅ ሀብት ለአምላክ ‘ታማኝ መሆናችንን’ በሚያሳይ መንገድ ልንጠቀምበት የሚገባ መሆኑን ነው። ይህን ማድረግ የምንችለው እንዴት ነው?
-