-
አርቆ በማሰብ ዕቅድ ማውጣትኢየሱስ—መንገድ፣ እውነት፣ ሕይወት
-
-
ኢየሱስ መጋቢው የተጠቀመበትን ዘዴ እየደገፈ ወይም ማጭበርበርን እያበረታታ አይደለም። ታዲያ ማስተማር የፈለገው ነገር ምንድን ነው? ደቀ መዛሙርቱን “በዓመፅ ሀብት ለራሳችሁ ወዳጆች አፍሩ፤ እነሱም የዓመፅ ሀብት ሲያልቅ በዘላለማዊ መኖሪያ ይቀበሏችኋል” በማለት አሳሰባቸው። (ሉቃስ 16:9) በእርግጥም አርቆ አሳቢና ብልህ መሆንን በተመለከተ ከዚህ ምሳሌ ጠቃሚ ትምህርት ማግኘት ይቻላል። ‘የብርሃን ልጆች’ የተባሉት የአምላክ አገልጋዮች ቁሳዊ ንብረታቸውን በጥበብ መጠቀማቸው ወደፊት የዘላለም ሕይወት ለማግኘት አጋጣሚ ይከፍትላቸዋል።
አንድ ሰው በሰማይ ያለውን መንግሥትም ሆነ በዚህ መንግሥት አስተዳደር ሥር በምድር ላይ የሚኖረውን ገነት እንዲወርስ ማድረግ የሚችሉት ይሖዋ አምላክ እና ልጁ ብቻ ናቸው። በመሆኑም ያለንን ቁሳዊ ንብረት ከመንግሥቱ ጋር የተያያዙ ጉዳዮችን ለማራመድ በመጠቀም ከይሖዋና ከልጁ ጋር ወዳጅነት ለመመሥረት ከፍተኛ ጥረት ማድረግ ይኖርብናል። ይህን ካደረግን ወርቅ፣ ብርና ሌሎች ቁሳዊ ነገሮች በሚያልቁበት ወይም በሚጠፉበት ጊዜ የዘላለም ሕይወት ማግኘታችን የተረጋገጠ ይሆናል።
-
-
አርቆ በማሰብ ዕቅድ ማውጣትኢየሱስ—መንገድ፣ እውነት፣ ሕይወት
-
-
ደቀ መዛሙርቱም “በዘላለማዊ መኖሪያ” የሚቀበላቸው ለማግኘት ከፈለጉ ተመሳሳይ ነገር እንደሚጠበቅባቸው ኢየሱስ መግለጹ ነው። አንድ ሰው፣ በአንድ በኩል የአምላክ እውነተኛ አገልጋይ በሌላ በኩል ደግሞ የዓመፃ ሀብት ባሪያ መሆን አይችልም። ኢየሱስ ሐሳቡን ሲደመድም እንዲህ ብሏል፦ “ለሁለት ጌቶች ባሪያ መሆን የሚችል አገልጋይ የለም፤ አንዱን ጠልቶ ሌላውን ይወዳል ወይም አንዱን ደግፎ ሌላውን ይንቃል። ለአምላክም ለሀብትም በአንድ ጊዜ ባሪያ መሆን አትችሉም።”—ሉቃስ 16:9, 13
-