-
የሀብታሙ ሰውና የአልዓዛር ሁኔታ ተለወጠኢየሱስ—መንገድ፣ እውነት፣ ሕይወት
-
-
ኢየሱስ እንዲህ አለ፦ “አንድ ሀብታም ሰው ነበር፤ ይህ ሰው ሐምራዊ ልብስና በፍታ ይለብስ የነበረ ከመሆኑም በላይ ዕለት ተዕለት በደስታና በቅንጦት ይኖር ነበር። ይሁን እንጂ እዚህ ሰው ደጃፍ ላይ እያመጡ የሚያስቀምጡት መላ ሰውነቱን ቁስል የወረሰው አልዓዛር የሚባል አንድ ለማኝ ነበር፤ እሱም ከሀብታሙ ማዕድ የሚወድቀውን ፍርፋሪ በልቶ ለመጥገብ ይመኝ ነበር። ውሾችም ሳይቀር እየመጡ ቁስሉን ይልሱ ነበር።”—ሉቃስ 16:19-21
-
-
የሀብታሙ ሰውና የአልዓዛር ሁኔታ ተለወጠኢየሱስ—መንገድ፣ እውነት፣ ሕይወት
-
-
ሀብታምና ኩሩ የሆኑት መሪዎች፣ ድሃ ለሆነው ተራ ሕዝብ ምን አመለካከት አላቸው? እነዚህን ሰዎች በንቀት አምሃአሬትስ ይኸውም የአገሬው (የመሬት) ሰዎች በማለት የሚጠሯቸው ሲሆን ሕጉን እንደማያውቁና ለመማርም ብቁ እንዳልሆኑ አድርገው ይመለከቷቸዋል። (ዮሐንስ 7:49) የእነዚህ ሰዎች ሁኔታ ‘አልዓዛር የተባለው ለማኝ’ ካለበት ሁኔታ ጋር ይመሳሰላል፤ አልዓዛር “ከሀብታሙ ማዕድ የሚወድቀውን ፍርፋሪ” እንኳ ለመብላት ይመኛል። መላ ሰውነቱን ቁስል እንደወረሰው እንደ አልዓዛር ሁሉ ተራው ሕዝብም በመንፈሳዊ ሁኔታ ሕመም ያለበት ያህል ዝቅ ተደርጎ ይታያል።
-