የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • ባዶ መቃብር—ኢየሱስ ሕያው ሆነ!
    ኢየሱስ—መንገድ፣ እውነት፣ ሕይወት
    • ሴቶቹ መቃብሩን ባዶ ሆኖ ሲያገኙት ምንኛ ደንግጠው ይሆን! መግደላዊቷ ማርያም “ወደ ስምዖን ጴጥሮስና ኢየሱስ ይወደው ወደነበረው ወደ ሌላው ደቀ መዝሙር” ይኸውም ወደ ሐዋርያው ዮሐንስ እየሮጠች ሄደች። (ዮሐንስ 20:2) መቃብሩ ቦታ የቀሩት ሌሎቹ ሴቶች ግን አንድ መልአክ አዩ። በመቃብሩ ውስጥ ደግሞ “ነጭ ልብስ የለበሰ” ሌላ መልአክ አለ።—ማርቆስ 16:5

  • ባዶ መቃብር—ኢየሱስ ሕያው ሆነ!
    ኢየሱስ—መንገድ፣ እውነት፣ ሕይወት
    • በዚህ ጊዜ ማርያም፣ ጴጥሮስንና ዮሐንስን አግኝታቸዋለች። ትንፋሿ እየተቆራረጠ “ጌታን ከመቃብሩ ውስጥ ወስደውታል፤ የት እንዳኖሩትም አናውቅም” አለቻቸው። (ዮሐንስ 20:2) ጴጥሮስና ዮሐንስም ይህን ሲሰሙ ወዲያውኑ መሮጥ ጀመሩ። ዮሐንስ ፈጣን በመሆኑ መቃብሩ ጋ ቀድሞ ደረሰ። ዮሐንስ ጎንበስ ብሎ ወደ ውስጥ ሲመለከት የበፍታ ጨርቆቹን አየ፤ ወደ ውስጥ ግን አልገባም።

      ጴጥሮስ ግን መቃብሩ ጋ ሲደርስ ሰተት ብሎ ወደ ውስጥ ገባ። በዚያም የበፍታ ጨርቆቹንና የኢየሱስ ራስ የተሸፈነበትን ጨርቅ ተመለከተ። በዚህ ጊዜ ዮሐንስም ወደ ውስጥ ገባ፤ ማርያም የነገረችውንም አመነ። ኢየሱስ አስቀድሞ የነገራቸው ቢሆንም አንዳቸውም ከሞት እንደተነሳ አልገባቸውም። (ማቴዎስ 16:21) በነገሩ ግራ ተጋብተው ወደ ቤት ተመለሱ። ወደ መቃብሩ ቦታ ተመልሳ የመጣችው ማርያም ግን እዚያው ቆየች።

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ