-
ባዶ መቃብር—ኢየሱስ ሕያው ሆነ!ኢየሱስ—መንገድ፣ እውነት፣ ሕይወት
-
-
በዚህ ጊዜ ማርያም፣ ጴጥሮስንና ዮሐንስን አግኝታቸዋለች። ትንፋሿ እየተቆራረጠ “ጌታን ከመቃብሩ ውስጥ ወስደውታል፤ የት እንዳኖሩትም አናውቅም” አለቻቸው። (ዮሐንስ 20:2) ጴጥሮስና ዮሐንስም ይህን ሲሰሙ ወዲያውኑ መሮጥ ጀመሩ። ዮሐንስ ፈጣን በመሆኑ መቃብሩ ጋ ቀድሞ ደረሰ። ዮሐንስ ጎንበስ ብሎ ወደ ውስጥ ሲመለከት የበፍታ ጨርቆቹን አየ፤ ወደ ውስጥ ግን አልገባም።
ጴጥሮስ ግን መቃብሩ ጋ ሲደርስ ሰተት ብሎ ወደ ውስጥ ገባ። በዚያም የበፍታ ጨርቆቹንና የኢየሱስ ራስ የተሸፈነበትን ጨርቅ ተመለከተ። በዚህ ጊዜ ዮሐንስም ወደ ውስጥ ገባ፤ ማርያም የነገረችውንም አመነ። ኢየሱስ አስቀድሞ የነገራቸው ቢሆንም አንዳቸውም ከሞት እንደተነሳ አልገባቸውም። (ማቴዎስ 16:21) በነገሩ ግራ ተጋብተው ወደ ቤት ተመለሱ። ወደ መቃብሩ ቦታ ተመልሳ የመጣችው ማርያም ግን እዚያው ቆየች።
-