-
አልዓዛር ከሞት ተነሳኢየሱስ—መንገድ፣ እውነት፣ ሕይወት
-
-
ቀያፋ፣ የሳንሄድሪን ሸንጎ ኢየሱስን ለመግደል እንዲወስን ማግባባት ቻለ። የኢየሱስ ወዳጅና የሳንሄድሪን ሸንጎ አባል የሆነው ኒቆዲሞስ ይህን ሴራ ለኢየሱስ ይነግረው ይሆን? ያም ሆነ ይህ ኢየሱስ፣ አምላክ ከወሰነው ጊዜ በፊት እንዳይሞት ሲል የኢየሩሳሌምን አካባቢ ለቆ ሄደ።
-
-
የሥጋ ደዌ የነበረበት ሰው አመስጋኝነት አሳየኢየሱስ—መንገድ፣ እውነት፣ ሕይወት
-
-
ኢየሱስ ከኢየሩሳሌም በስተ ሰሜን ምሥራቅ ወደምትገኘው ኤፍሬም የተባለች ከተማ ተጓዘ፤ በመሆኑም የሳንሄድሪን ሸንጎ እሱን ለመግደል ያወጣው ዕቅድ ከሸፈ። ኢየሱስ ከጠላቶቹ ርቆ ከደቀ መዛሙርቱ ጋር በዚህች ከተማ ተቀመጠ። (ዮሐንስ 11:54) ይሁን እንጂ በ33 ዓ.ም. የሚከበረው የፋሲካ በዓል እየተቃረበ በመሆኑ ኢየሱስ ብዙም ሳይቆይ እንደገና መጓዝ ጀመረ። ሰማርያን አቋርጦ በስተ ሰሜን ወደ ገሊላ ተጓዘ፤ ይህ ከመሞቱ በፊት ወደዚህ አካባቢ ያደረገው የመጨረሻ ጉዞው ነው።
-