-
በአምላክም ሆነ በሰው ፊት ክቡር የሆነ የጋብቻ ሥነ ሥርዓትመጠበቂያ ግንብ—2006 | ጥቅምት 15
-
-
3. ኢየሱስ በቃና ለየትኛው ዝግጅት አስተዋጽኦ አድርጓል?
3 በእስራኤላውያን ዘንድ እንደ ሠርግ የሚቆጠረው ይህ ድርጊት ነበር። ከዚያ በኋላ በዮሐንስ 2:1 ላይ ተመዝግቦ እንደሚገኘው ዓይነት ድግስ ይደረግ ይሆናል። በርካታ የመጽሐፍ ቅዱስ ትርጉሞች ይህንን ጥቅስ “በቃና ከተማ ሰርግ ነበር” ብለው ተርጉመውታል። ሆኖም በኩረ ጽሑፉ እዚህ ላይ የተጠቀመበት ቃል በሌሎች ቦታዎች ‘የሰርግ ድግስ’ ወይም ‘የሰርግ ግብዣ’ ተብሎ ይበልጥ ተስማሚ በሆነ መንገድ ተተርጉሟል።a (ማቴዎስ 22:2-10፤ 25:10፤ ሉቃስ 14:8 የ1980 ትርጉም) ከዘገባው በግልጽ መረዳት እንደሚቻለው ኢየሱስ ከአይሁዳውያን ሠርግ ጋር በተያያዘ ተዘጋጅቶ በነበረ አንድ ድግስ ላይ የተገኘ ሲሆን ግብዣው የበለጠ አስደሳች እንዲሆንም አስተዋጽኦ አድርጓል። ይሁን እንጂ በዚያን ጊዜ የነበረ ሠርግ የሚያካትታቸው ነገሮች በዛሬው ጊዜ ከተለመደው የጋብቻ ሥነ ሥርዓት የተለዩ እንደሆኑ ልብ ልንል ይገባል።
-