የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • jy ምዕ. 16 ገጽ 42-ገጽ 43 አን. 8
  • ለእውነተኛው አምልኮ ቅንዓት አሳየ

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • ለእውነተኛው አምልኮ ቅንዓት አሳየ
  • ኢየሱስ—መንገድ፣ እውነት፣ ሕይወት
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • ለይሖዋ አምልኮ ያሳየው ቅንዓት
    እስከ ዛሬ ከኖሩት ሁሉ የሚበልጠው ታላቅ ሰው
  • ኢየሱስ ነጋዴዎችን ከቤተ መቅደሱ አባረረ
    ከመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች ምን ትማራለህ?
  • በቃና የፈጸመው ሁለተኛ ተአምር
    ኢየሱስ—መንገድ፣ እውነት፣ ሕይወት
  • ኢየሱስ የፈጸመው የመጀመሪያ ተአምር
    ኢየሱስ—መንገድ፣ እውነት፣ ሕይወት
ለተጨማሪ መረጃ
ኢየሱስ—መንገድ፣ እውነት፣ ሕይወት
jy ምዕ. 16 ገጽ 42-ገጽ 43 አን. 8
ኢየሱስ ገንዘብ መንዛሪዎቹን ከቤተ መቅደሱ ሲያባርራቸው

ምዕራፍ 16

ለእውነተኛው አምልኮ ቅንዓት አሳየ

ዮሐንስ 2:12-22

  • ኢየሱስ ቤተ መቅደሱን አጸዳ

በቃና ከተካሄደው ሠርግ በኋላ ኢየሱስ ወደ ቅፍርናሆም አቀና። እናቱና ወንድሞቹ ያዕቆብ፣ ዮሴፍ፣ ስምዖንና ይሁዳም አብረውት ናቸው።

ኢየሱስ ወደ ቅፍርናሆም የሄደው ለምንድን ነው? ይህች ከተማ ከናዝሬት ወይም ከቃና ይበልጥ አማካይ ቦታ ላይ የምትገኝ ከመሆኗም ሌላ ሰፊ ሳትሆን አትቀርም። በተጨማሪም ከኢየሱስ አዳዲስ ደቀ መዛሙርት አብዛኞቹ የሚኖሩት በቅፍርናሆም ወይም በአቅራቢያዋ ነው። ስለዚህ ኢየሱስ በመኖሪያ አካባቢያቸው እያሉ ሊያሠለጥናቸው ይችላል።

ኢየሱስ በቅፍርናሆም በቆየባቸው ጊዜያትም አስደናቂ ነገሮችን ፈጽሟል። በመሆኑም በዚህች ከተማና በአካባቢዋ የሚኖሩ ብዙ ሰዎች ኢየሱስ ስላደረጋቸው ነገሮች ሰሙ። ብዙም ሳይቆይ ግን ኢየሱስና የአይሁድን እምነት አጥብቀው የሚከተሉት ወዳጆቹ፣ በ30 ዓ.ም. በሚከበረው የፋሲካ በዓል ላይ ለመገኘት ወደ ኢየሩሳሌም መሄድ አለባቸው።

ደቀ መዛሙርቱ በኢየሩሳሌም ባለው ቤተ መቅደስ ሳሉ ከዚህ ቀደም አይተው የማያውቁትን አስገራሚ የሆነ የኢየሱስ ባሕርይ ተመለከቱ።

የአምላክ ሕግ በሚያዘው መሠረት እስራኤላውያን በቤተ መቅደሱ የእንስሳት መሥዋዕት ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል፤ ወደ ቤተ መቅደሱ የሚመጡ ሰዎችም በዚያ በሚቆዩበት ጊዜ ምግብ ያስፈልጋቸዋል። በመሆኑም ራቅ ካሉ ቦታዎች ወደ ኢየሩሳሌም የሚመጡ ሰዎች ገንዘብ ይዘው በመሄድ “ከብት፣ በግ፣ ፍየል” እንዲሁም በከተማዋ ሲቆዩ የሚያስፈልጓቸውን ሌሎች ነገሮች እዚያ እንዲገዙ ሕጉ ይፈቅዳል። (ዘዳግም 14:24-26) በኢየሩሳሌም የነበሩ ነጋዴዎች በቤተ መቅደሱ ሰፊ ግቢ ውስጥ እንስሳትንና ወፎችን ይሸጣሉ። አንዳንዶቹ ግን ሕዝቡን ከፍተኛ ዋጋ በማስከፈል ያጭበረብራሉ።

ኢየሱስ በዚህ በጣም በመናደዱ የገንዘብ ለዋጮቹን ሳንቲሞች በተነ፣ ጠረጴዛዎቻቸውን ገለባበጠ እንዲሁም ሰዎቹን አባረራቸው። ከዚያም “እነዚህን ከዚህ አስወጡ! የአባቴን ቤት የንግድ ቤት ማድረጋችሁ ይብቃ!” አላቸው።—ዮሐንስ 2:16

የኢየሱስ ደቀ መዛሙርት ይህን ሲመለከቱ “ለቤትህ ያለኝ ቅንዓት ይበላኛል” የሚለውን ስለ አምላክ ልጅ የተነገረ ትንቢት አስታወሱ። አይሁዳውያን ግን “እነዚህን ነገሮች ለማድረግ ሥልጣን እንዳለህ የሚያረጋግጥ ምን ምልክት ታሳየናለህ?” ብለው ጠየቁት። ኢየሱስም “ይህን ቤተ መቅደስ አፍርሱት፤ እኔም በሦስት ቀን ውስጥ አነሳዋለሁ” ሲል መለሰላቸው።—ዮሐንስ 2:17-19፤ መዝሙር 69:9

አይሁዳውያኑ፣ ኢየሱስ ቃል በቃል ስለ ቤተ መቅደሱ የተናገረ ስለመሰላቸው “ቤተ መቅደሱን ለመገንባት 46 ዓመት ፈጅቷል፤ ታዲያ አንተ በሦስት ቀን ታነሳዋለህ?” አሉት። (ዮሐንስ 2:20) ኢየሱስ ግን ቤተ መቅደስ ሲል ስለ ራሱ ሰውነት መናገሩ ነበር። ከሦስት ዓመት በኋላ ኢየሱስ ከሞት ሲነሳ ደቀ መዛሙርቱ ይህን ቃል አስታወሱ።

  • ኢየሱስ በቃና በተደረገው ሠርግ ላይ ከተገኘ በኋላ ወደ የትኞቹ ቦታዎች ሄደ?

  • ኢየሱስ በቤተ መቅደሱ ውስጥ በተመለከተው ነገር የተናደደው ለምንድን ነው? ምንስ አደረገ?

  • ኢየሱስ “ይህን ቤተ መቅደስ” ሲል ምን ማመልከቱ ነው? የተናገረው ነገር ምን ትርጉም አለው?

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ