-
ሳውል ክርስቲያኖችን ያሳደደው ለምን ነበር?መጠበቂያ ግንብ—1999 | ሰኔ 15
-
-
ደማስቆ ከኢየሩሳሌም 220 ኪሎ ሜትር ማለትም የሰባት ወይም የስምንት ቀን የእግር መንገድ ያህል ርቃ ትገኛለች። ቢሆንም ግን ሳውል “ደቀ መዛሙርት[ን] እንዲገድላቸው ገና እየዛተ” ወደ ሊቀ ካህኑ ሄደና በደማስቆ ላሉት ምኩራቦች ደብዳቤ እንዲጽፍለት ጠየቀው። ለምን? ሳውል በዚህ “መንገድ” ያለን ማንኛውንም ሰው እያሰረ ወደ ኢየሩሳሌም ለማምጣት እንዲችል ነው። ሳውልም በተሰጠው ሥልጣን መሠረት ‘ቤተ ክርስቲያንን እያፈረሰ ወደ ሁሉም ቤት እየገባ ወንዶችንም ሴቶችንም እየጎተተ ወደ ወህኒ ይሰጥ’ ነበር። ሌሎቹንም ‘ወደየምኩራቡ እየጎተተ’ እና ‘ድምፁን እየሰጠ’ (ቃል በቃል “የድምፅ መስጫ ጠጠር በመጣል”) እንዲገደሉ ደግፏል።—ሥራ 8:3፤ 9:1, 2, 14፤ 22:5, 19፤ 26:10፣ የአዲሲቱ ዓለም ትርጉም የግርጌ ማስታወሻ
አንዳንድ ምሁራን ሳውል ከገማልያል የተማረውን ትምህርትና አሁን ያገኘውን ሥልጣን ከግምት ውስጥ በማስገባት ከተራ የሕግ ተማሪነት ተነስቶ በአይሁድ ማህበረሰብ ውስጥ ከፍተኛ ሥልጣን እስከመያዝ ደርሷል ብለው ያምናሉ። ለምሳሌ አንድ ጸሐፊ ምናልባት ሳውል በኢየሩሳሌም ምኩራብ አስተማሪ ሳይሆን አልቀረም ብለው ገምተዋል። ይሁን እንጂ እዚህ ላይ ሳውል ‘ድምፁን እየሰጠ’ ሲል በችሎት አባልነት ማለቱ ይሁን ወይም ክርስቲያኖች እንዲገደሉ በግሰብ ደረጃ የሞራል ድጋፍ ሰጠ ማለቱ በእርግጠኝነት መናገር አንችልም።a
-
-
ሳውል ክርስቲያኖችን ያሳደደው ለምን ነበር?መጠበቂያ ግንብ—1999 | ሰኔ 15
-
-
a በኤሚል ሹረር የተዘጋጀው ዘ ሂስትሪ ኦቭ ዘ ጅዊሽ ፒፕል ኢን ዚ ኤጅ ኦቭ ጂሰስ ክራይስት (175ከዘአበ-135እዘአ) የተባለው መጽሐፍ እንደሚለው ከሆነ ምንም እንኳን በሚሽናህ ላይ ስለ ታላቁ ሳንሄድሪን ወይም ሰባ አንድ አባላት ስላሉት ሳንሄድሪን ምንም የተዘገበ ነገር ባይኖርም 23 አባሎች ስላሏቸው ስለ ትንንሾቹ ሳንሄድሪኖች ግን ጥቃቅን ዝርዝሮች እንኳን ተገልጸዋል። የሕግ ተማሪዎች በትንንሾቹ ሳንሄድሪኖች በሚታዩት ከባባድ ጉዳዮች ላይ ለመካፈልና ተከሳሹን በመቃወም ሳይሆን በመደገፍ ለመናገር እንዲችሉ ይፈቀድላቸው ነበር። ከባባድ ባልሆኑ ጉዳዮች ላይ ግን ሁለቱንም ማድረግ ይችሉ ነበር።
-