-
“በባሕር ፍርሃት”መጠበቂያ ግንብ—1999 | መጋቢት 15
-
-
የሮም የምግብ አቅርቦትም በመርከብ ትራንስፖርት ኢንዱስትሪ ላይ የተመካ ነበር። ወደ አንድ ሚልዮን የሚጠጋ ሕዝብ የነበራት ሮም በዓመት ከ250,000 እስከ 400,000 ቶን የሚጠጋ ከፍተኛ የእህል ፍጆታ ነበራት። ይህን ያህል ብዛት ያለው እህል ይመጣ የነበረው ከየት ነው? ሰሜን አፍሪካ በዓመት ውስጥ ስምንቱን ወራት ለሮም የሚያስፈልገውን ምግብ ስታቀርብ ግብፅ ደግሞ ለተቀሩት አራት ወራት ለከተማዋ የሚያስፈልገውን እህል በበቂ መጠን እንደምታቀርብ ዳግማዊ ሄሮድስ አግሪጳ መናገሩን ፍላቪየስ ጆሴፈስ ጠቅሷል። ለዚህች ከተማ እህል በማቅረብ ሥራ ላይ የተሰማሩ በሺዎች የሚቆጠሩ መርከቦች ነበሩ።
-
-
“በባሕር ፍርሃት”መጠበቂያ ግንብ—1999 | መጋቢት 15
-
-
ጳውሎስ ተሳፍሮበት ስለነበረውና ማልታ ላይ ስለተሰባበረው መርከብ ምን የሚታወቅ ነገር አለ? መርከቡ እህል የጫነ ሲሆን ‘ወደ ኢጣሊያ የሚሄድ የእስክንድርያ መርከብ’ ነበር። (ሥራ 27:6፣ የአዲሲቱ ዓለም ትርጉም የግርጌ ማስታወሻ) እህል ተሸካሚ መርከቦቹ የግሪካውያን፣ የፊንቃውያንና የሶርያውያን የግል ንብረቶች ሲሆኑ አመራር የሚያገኙትም ሆነ ዕቃዎች የሚሟሉላቸው በእነርሱ አማካኝነት ነበር። ሆኖም የሮም መንግሥት መርከቦቹን ይከራይ ነበር። ታሪክ ጸሐፊው ዊልያም ኤም ራምሴይ እንዲህ ሲሉ ተናግረዋል:- “ከቀረጥ አሰባሰብ ጋር ተመሳሳይ በሆነ መንገድ መንግሥት ራሱ ለዚህ ሰፊ አገልግሎት በሰው ኃይልና በመሣሪያ ረገድ የሚያስፈልገውን ግዙፍ መዋቅር ከማደራጀት ይልቅ ሥራውን በኮንትራት መልክ መስጠቱን ይበልጥ ቀላል ሆኖ አግኝቶታል።”
-