-
“ከእናንተ አንድም ሰው አይጠፋም”‘ስለ አምላክ መንግሥት በሚገባ መመሥከር’
-
-
“ሁሉም በደህና ወደ የብስ ደረሱ” (የሐዋርያት ሥራ 27:27-44)
“በሁሉ ፊት አምላክን አመሰገነ።”—የሐዋርያት ሥራ 27:35
16, 17. (ሀ) ጳውሎስ የጸለየው የትኛውን አጋጣሚ ተጠቅሞ ነው? ይህስ ምን ውጤት አስገኘ? (ለ) ጳውሎስ የተናገረው ነገር የተፈጸመው እንዴት ነው?
16 መርከቡ አስፈሪ በሆኑት ሁለት ሳምንታት ውስጥ 870 ኪሎ ሜትር ገደማ በነፋስ እየተገፋ ሄዷል፤ አሁን ግን መርከበኞቹ የሆነ ለውጥ አስተዋሉ፤ ምናልባትም ውኃ ከመሬት ጋር ሲላተም የሚፈጥረውን ድምፅ ሰምተው ሊሆን ይችላል። ከፊት ለፊታቸው የብስ ካለም ወደዚያ ለማምራት አሰቡ፤ ስለዚህ ከኋላ ያሉትን መልሕቆች በመጣል መርከቡ ካሉበት ቦታ እየተገፋ እንዳይሄድ፣ የፊተኛው ክፍልም ወደ የብሱ አቅጣጫ እንዲሆን ለማድረግ ሞከሩ። በዚህ ጊዜ መርከበኞቹ መርከቡን ጥለው ለማምለጥ ሞክረው ነበር፤ ወታደሮቹ ግን እንዳይሄዱ ከለከሏቸው። ጳውሎስ መኮንኑንና ወታደሮቹን “እነዚህ ሰዎች መርከቡን ጥለው ከሄዱ ልትድኑ አትችሉም” አላቸው። መርከቡ ትንሽ ከተረጋጋ በኋላ ጳውሎስ ምግብ እንዲበሉ አበረታታቸው፤ ሁሉም እንደሚተርፉም በድጋሚ ነገራቸው። ከዚያም “በሁሉ ፊት አምላክን አመሰገነ።” (ሥራ 27:31, 35) ጳውሎስ ያቀረበው ይህ የምስጋና ጸሎት ለሉቃስም ሆነ ለአርስጥሮኮስ እንዲሁም ዛሬ ላሉ ክርስቲያኖች ግሩም ምሳሌ ይሆናል። አንተስ በሌሎች ሰዎች ፊት የምታቀርበው ጸሎት ሰሚዎቹን የሚያበረታታና የሚያጽናና ነው?
-