የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • “ከእናንተ አንድም ሰው አይጠፋም”
    ‘ስለ አምላክ መንግሥት በሚገባ መመሥከር’
    • “ሁሉም በደህና ወደ የብስ ደረሱ” (የሐዋርያት ሥራ 27:27-44)

      ጳውሎስ በመንገደኞች በተጨናነቀው የዕቃ መጫኛ መርከብ ላይ ሆኖ ሲጸልይ። ጉዞው ያዛላቸው አንዳንድ መንገደኞች አቀርቅረው ሲጸልዩ ሌሎች ደግሞ ሁኔታውን እየተመለከቱ ነው። ከፊት ለፊታቸው ቂጣ ቀርቧል።

      “በሁሉ ፊት አምላክን አመሰገነ።”—የሐዋርያት ሥራ 27:35

      16, 17. (ሀ) ጳውሎስ የጸለየው የትኛውን አጋጣሚ ተጠቅሞ ነው? ይህስ ምን ውጤት አስገኘ? (ለ) ጳውሎስ የተናገረው ነገር የተፈጸመው እንዴት ነው?

      16 መርከቡ አስፈሪ በሆኑት ሁለት ሳምንታት ውስጥ 870 ኪሎ ሜትር ገደማ በነፋስ እየተገፋ ሄዷል፤ አሁን ግን መርከበኞቹ የሆነ ለውጥ አስተዋሉ፤ ምናልባትም ውኃ ከመሬት ጋር ሲላተም የሚፈጥረውን ድምፅ ሰምተው ሊሆን ይችላል። ከፊት ለፊታቸው የብስ ካለም ወደዚያ ለማምራት አሰቡ፤ ስለዚህ ከኋላ ያሉትን መልሕቆች በመጣል መርከቡ ካሉበት ቦታ እየተገፋ እንዳይሄድ፣ የፊተኛው ክፍልም ወደ የብሱ አቅጣጫ እንዲሆን ለማድረግ ሞከሩ። በዚህ ጊዜ መርከበኞቹ መርከቡን ጥለው ለማምለጥ ሞክረው ነበር፤ ወታደሮቹ ግን እንዳይሄዱ ከለከሏቸው። ጳውሎስ መኮንኑንና ወታደሮቹን “እነዚህ ሰዎች መርከቡን ጥለው ከሄዱ ልትድኑ አትችሉም” አላቸው። መርከቡ ትንሽ ከተረጋጋ በኋላ ጳውሎስ ምግብ እንዲበሉ አበረታታቸው፤ ሁሉም እንደሚተርፉም በድጋሚ ነገራቸው። ከዚያም “በሁሉ ፊት አምላክን አመሰገነ።” (ሥራ 27:31, 35) ጳውሎስ ያቀረበው ይህ የምስጋና ጸሎት ለሉቃስም ሆነ ለአርስጥሮኮስ እንዲሁም ዛሬ ላሉ ክርስቲያኖች ግሩም ምሳሌ ይሆናል። አንተስ በሌሎች ሰዎች ፊት የምታቀርበው ጸሎት ሰሚዎቹን የሚያበረታታና የሚያጽናና ነው?

  • “ከእናንተ አንድም ሰው አይጠፋም”
    ‘ስለ አምላክ መንግሥት በሚገባ መመሥከር’
    • እርግጥ በሐዋርያት ሥራ 27:27 ላይ ‘የአድርያ ባሕር’ ተጠቅሷል፤ ይሁንና በጳውሎስ ዘመን “አድርያ” የሚለው ቃል ዛሬ ከሚታወቀው የአድሪያቲክ ባሕር የበለጠ ሰፊ ቦታ ይሸፍን ነበር። ይህ መጠሪያ የአዮንያን ባሕርን እንዲሁም ከሲሲሊ በስተ ምሥራቅና ከቀርጤስ በስተ ምዕራብ የሚገኙ የውኃ አካላትን ያጠቃልላል፤ በዛሬዋ ማልታ ዙሪያ ያለው ባሕርም ያኔ የአድርያ ባሕር ክፍል ነበር።

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ