-
ጳውሎስ የደረሰበትን መከራ በድል ተወጣመጠበቂያ ግንብ—1999 | ግንቦት 1
-
-
ዓውሎ ነፋሱ በያዛቸው በ14ኛው ቀን መርከበኞቹ የውኃው ጥልቀት ሀያ አክናድ ብቻ መሆኑን ሲገነዘቡ ተደሰቱ።a ጥቂት ርቀት ከተጓዙ በኋላ እንደገና መለኪያ ገመድ ጣሉ። በዚህ ጊዜ ጥልቀቱ 15 አክናድ ሆኖ ተገኘ። ወደ የብስ ተቃርበዋል! ሆኖም ይህ ምሥራች የራሱ የሆነ ሊጤን የሚገባው አንድምታ አለው። መርከቡ ጥልቀት በሌለው ውኃ ላይ በጨለማ ወዲያና ወዲህ ሲንሳፈፍ ከዓለት ጋር ተላትሞ የመሰባበር አደጋ ሊያጋጥመው ይችላል። መርከበኞቹ መልሕቆቹን መጣላቸው ጥበብ ያለበት እርምጃ ነበር። ከእነርሱ መካከል አንዳንዶቹ ለመጠባበቂያ የተዘጋጀችውን ታንኳ አውርደው እንደምንም በባሕሩ ላይ ለመቅዘፍ አሰቡ።b ሆኖም ጳውሎስ ለጦር መኮንኑና ለወታደሮቹ “እነዚህ በመርከቡ ካልቆዩ እናንተ ትድኑ ዘንድ አትችሉም” ብሎ በመንገር እንዳይሄዱ አገዳቸው። መኮንኑ በጳውሎስ ሐሳብ በመስማማቱ በመርከቡ ላይ ያሉት 276 ተሳፋሪዎች በሙሉ ጎሕ እስኪቀድ ድረስ በጭንቀት ተውጠው መጠባበቅ ያዙ።—ሥራ 27:27-32
-
-
ጳውሎስ የደረሰበትን መከራ በድል ተወጣመጠበቂያ ግንብ—1999 | ግንቦት 1
-
-
b ታንኳ፣ አንድ መርከብ በባሕር ዳርቻ መልሕቁን ሲጥል ወደ የብስ ለመውጣት የሚያገለግል ትንሽ ጀልባ ነው። በግልጽ መረዳት እንደሚቻለው መርከበኞቹ እዚያው የሚቀሩትን መርከብ መንዳት የማይችሉ ሰዎች ጥለው የራሳቸውን ሕይወት ለማዳን ሙከራ ማድረጋቸው ነበር።
-