-
“ከእናንተ አንድም ሰው አይጠፋም”‘ስለ አምላክ መንግሥት በሚገባ መመሥከር’
-
-
“የተለየ ደግነት” (የሐዋርያት ሥራ 28:1-10)
18-20. የማልታ ነዋሪዎች “የተለየ ደግነት” ያሳዩት እንዴት ነው? አምላክ በጳውሎስ አማካኝነት ምን ተአምር ፈጸመ?
18 ከአደጋው የተረፉት ሰዎች ከሲሲሊ በስተ ደቡብ ማልታ በተባለች ደሴት ላይ እንደሚገኙ ተገነዘቡ። (“ማልታ የምትገኘው የት ነው?” የሚለውን ሣጥን ተመልከት።) ባዕድ ቋንቋ የሚናገሩት የደሴቲቱ ነዋሪዎች “የተለየ ደግነት” አሳዩአቸው። (ሥራ 28:2) የማልታ ሰዎች በውኃ ርሰውና በብርድ እየተንቀጠቀጡ ለመጡት እንግዶች እሳት አነደዱላቸው። ብርዱና ዝናቡ ባያቆምም እሳቱ ሞቅ አደረጋቸው። በተጨማሪም አንድ ተአምር እንዲፈጸም ምክንያት ሆነ።
-