-
‘ነገር ሁሉ የሚታደስበት ዘመን’ ቀርቧል!መጠበቂያ ግንብ—2000 | መስከረም 1
-
-
ይህንን ሥራ በጥቂት ቀናት፣ ሳምንታት ወይም ወራት ውስጥ ሠርቶ መጨረስ አይቻልም። ቢሆንም ደቀ መዛሙርቱ ወዲያውኑ መስበክ ጀመሩ። ያም ሆኖ ግን መንግሥቱ ስለሚመለስበት ጊዜ ለማወቅ የነበራቸው ፍላጎት አልጠፋም። ሐዋርያው ጴጥሮስ ይህንን አስመልክቶ በኢየሩሳሌም ተሰብስቦ ለነበረው ብዙ ሕዝብ የሚከተለውን ተናግሯል:- “ከጌታ ፊት የመጽናናት ዘመን እንድትመጣላችሁ አስቀድሞም ለእናንተ የመረጠውን ኢየሱስ ክርስቶስን እንዲልክላችሁ፣ ኃጢአታችሁ ይደመሰስ ዘንድ ንስሐ ግቡ ተመለሱም። እግዚአብሔር ከጥንት ጀምሮ በቅዱሳን ነቢያቱ አፍ የተናገረው፣ ነገር ሁሉ እስከሚታደስበት ዘመን ድረስ ሰማይ ይቀበለው ዘንድ ይገባልና።”—ሥራ 3:19-21፣ በሰያፍ የጻፍነው እኛ ነን።
ይህ ‘ነገር ሁሉ የሚታደስበት ዘመን’ የሚመጣው በይሖዋ “የመጽናናት ዘመን” ውስጥ ነው። ነገር ሁሉ እንደሚታደስ አስቀድሞ የተነገረው ትንቢት ፍጻሜውን የሚያገኘው በሁለት መልኩ ነው። አንዱ አስደሳች በሆነው መንፈሳዊ ተሐድሶ አማካኝነት ሲሆን ይህም በዛሬው ጊዜ በመከናወን ላይ ይገኛል። ሁለተኛው ደግሞ ይህን ተሐድሶ ተከትሎ በሚቋቋመው ምድራዊ ገነት ወቅት ፍጻሜውን ያገኛል።
-
-
‘ነገር ሁሉ የሚታደስበት ዘመን’ ቀርቧል!መጠበቂያ ግንብ—2000 | መስከረም 1
-
-
አሕዛብ ሁሉ ክርስቶስ ተከታዮቹ እንዲያደርጉት ያዘዘውን ነገር እንዲጠብቁ ለማስተማር መጠነ ሰፊ ዘመቻ ተካሂዷል። (ማቴዎስ 28:20) ቀድሞ የእንስሳ ዓይነት ባህርይ ያሳዩ የነበሩ ሰዎች አሁን አመለካከታቸውን ለውጠው ማየት እንዴት መንፈስን ያድሳል! እንዲህ ያሉት ሰዎች እንደ “ንዴት፣” “ስድብ” እንዲሁም “የሚያሳፍር ንግግር” የመሳሰሉትን ባሕርያት እንዲያንጸባርቁ ተጽእኖ ያደረገባቸውን አሮጌ ሰው አውልቀው በመጣል “የፈጠረውንም ምሳሌ [አምላክን] እንዲመስል እውቀትን ለማግኘት የሚታደሰውን አዲሱን ሰው” ለብሰዋል። ነቢዩ ኢሳይያስ የተናገራቸው ቃላት አሁንም እንኳ በመንፈሳዊ ሁኔታ ፍጻሜያቸውን እያገኙ ነው:- “ተኩላ [ቀድሞ የተኩላ ዓይነት ባሕርይ የነበረው ሰው] ከበግ ጠቦት [የየዋህነት ባሕርይ ከሚያሳይ ሰው] ጋር ይቀመጣል፣ ነብርም ከፍየል ጠቦት ጋር ይተኛል፤ ጥጃና የአንበሳ ደቦል ፍሪዳም በአንድነት ያርፋሉ።”—ቆላስይስ 3:8-10፤ ኢሳይያስ 11:6, 9
-