-
‘ነገር ሁሉ የሚታደስበት ዘመን’ ቀርቧል!መጠበቂያ ግንብ—2000 | መስከረም 1
-
-
ይህንን ሥራ በጥቂት ቀናት፣ ሳምንታት ወይም ወራት ውስጥ ሠርቶ መጨረስ አይቻልም። ቢሆንም ደቀ መዛሙርቱ ወዲያውኑ መስበክ ጀመሩ። ያም ሆኖ ግን መንግሥቱ ስለሚመለስበት ጊዜ ለማወቅ የነበራቸው ፍላጎት አልጠፋም። ሐዋርያው ጴጥሮስ ይህንን አስመልክቶ በኢየሩሳሌም ተሰብስቦ ለነበረው ብዙ ሕዝብ የሚከተለውን ተናግሯል:- “ከጌታ ፊት የመጽናናት ዘመን እንድትመጣላችሁ አስቀድሞም ለእናንተ የመረጠውን ኢየሱስ ክርስቶስን እንዲልክላችሁ፣ ኃጢአታችሁ ይደመሰስ ዘንድ ንስሐ ግቡ ተመለሱም። እግዚአብሔር ከጥንት ጀምሮ በቅዱሳን ነቢያቱ አፍ የተናገረው፣ ነገር ሁሉ እስከሚታደስበት ዘመን ድረስ ሰማይ ይቀበለው ዘንድ ይገባልና።”—ሥራ 3:19-21፣ በሰያፍ የጻፍነው እኛ ነን።
-
-
‘ነገር ሁሉ የሚታደስበት ዘመን’ ቀርቧል!መጠበቂያ ግንብ—2000 | መስከረም 1
-
-
ሐዋርያው ጴጥሮስ በኢየሩሳሌም ለተሰበሰበው ብዙ ሕዝብ እንደተናገረው ሰማይ ኢየሱስን ‘ተቀብሎታል።’ ይህ ሁኔታ ኢየሱስ በ1914 በንጉሣዊ ሥልጣኑ ላይ በመገኘት በአምላክ የተሾመ ንጉሥ ሆኖ መግዛት እስከጀመረበት ጊዜ ድረስ ቀጥሏል። ጴጥሮስ አስቀድሞ እንደተናገረው በ1914 በአምላክ ዓላማ ውስጥ ቁልፍ ሚና የሚጫወተው ኢየሱስ የድርሻውን እንዲያከናውን በመፍቀድ ይሖዋ ልጁን ‘ልኳል’ ሊባል ይችላል። መጽሐፍ ቅዱስ ሁኔታውን ምሳሌያዊ በሆነ መንገድ እንዲህ ሲል ይገልጸዋል:- “[የአምላክ ሰማያዊ ድርጅት] አሕዛብንም ሁሉ በብረት በትር ይገዛቸው ዘንድ ያለውን ልጅ ወንድ ልጅ [በኢየሱስ ክርስቶስ የሚመራውን የአምላክ መንግሥት] ወለደች።”—ራእይ 12:5
-