የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • w20 መጋቢት ገጽ 31
  • የአንባቢያን ጥያቄዎች

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • የአንባቢያን ጥያቄዎች
  • የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2020
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • የፖሊስ ጥበቃ—የሚያሳድረው ተስፋና የሚፈጥረው ሥጋት
    ንቁ!—2002
  • ‘የአይሁድን ሸንጎ በአንድነት ሰበሰቡ’
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2006
  • የአንባብያን ጥያቄዎች
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2002
  • ፖሊሶች—አስፈላጊ የሆኑት ለምንድን ነው?
    ንቁ!—2002
ለተጨማሪ መረጃ
የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2020
w20 መጋቢት ገጽ 31
የአይሁድ የቤተ መቅደስ ፖሊሶች ሁለት ሰዎችን በሃይማኖታቸው ምክንያት ሲያስሩ።

የአንባቢያን ጥያቄዎች

የአይሁድ የቤተ መቅደስ ፖሊሶች እነማን ነበሩ? ሥራቸውስ ምን ነበር?

ካህናት ያልሆኑ ሌዋውያን ከሚያከናውኗቸው በርካታ ሥራዎች መካከል አንዱ ከፖሊስ ሥራ ጋር ይመሳሰል ነበር። ይህን ሥራ የሚያከናውኑት በቤተ መቅደሱ ሹም አመራር ሥር ሆነው ነው። የአይሁድ ታሪክ ጸሐፊ የሆነው ፋይሎ የእነዚህን ጠባቂዎች ሥራ ሲገልጽ እንዲህ ብሏል፦ “ከእነዚህ [ሌዋውያን] መካከል አንዳንዶቹ በመግቢያው ላይ ዘብ ሆነው ይቆሙ ነበር፤ አንዳንዶቹ ደግሞ [በቤተ መቅደሱ] ውስጥ ከመቅደሱ ፊት ለፊት በመቆም ያልተፈቀደለት ሰው፣ በማወቅም ሆነ ባለማወቅ ወደዚያ እንዳይገባ ይከላከሉ ነበር። ሌሎቹ ደግሞ በፈረቃ ቀንና ሌሊት ቤተ መቅደሱን እየዞሩ ይጠብቁ ነበር።”

የሳንሄድሪን ሸንጎ እነዚህን ፖሊሶች ማዘዝ ይችል ነበር። ሮማውያን መሣሪያ እንዲታጠቅ የሚፈቅዱለት የአይሁዳውያን ቡድን ይህ ብቻ ነበር።

ዮአኪም ዬርምያስ የተባሉ ምሁር እንዲህ ብለዋል፦ “ኢየሱስ በተያዘበት ወቅት ለሰዎቹ በየዕለቱ በቤተ መቅደስ ሲያስተምር ያልያዙት ለምን እንደሆነ የጠየቃቸው (ማቴ. 26:55) ሊይዙት የመጡት ሰዎች የቤተ መቅደሱ ፖሊሶች ስለሆኑ መሆን አለበት።” እኚህ ጸሐፊ ከተወሰነ ጊዜ በፊት ኢየሱስን ለመያዝ የተላኩት ሰዎችም የቤተ መቅደስ ፖሊሶች እንደሆኑ ያምናሉ። (ዮሐ. 7:32, 45, 46) ከጊዜ በኋላም ፖሊሶቹና የቤተ መቅደሱ ሹም የኢየሱስን ደቀ መዛሙርት ወደ ሳንሄድሪን ሸንጎ ይዘው እንዲመጡ ተልከው ነበር፤ ሐዋርያው ጳውሎስንም ከቤተ መቅደሱ ጎትተው ያወጡት እነሱ ሳይሆኑ አይቀሩም።—ሥራ 4:1-3፤ 5:17-27፤ 21:27-30

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ