የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • “አምላክን እንደ ገዢያችን አድርገን ልንታዘዝ ይገባል”
    ‘ስለ አምላክ መንግሥት በሚገባ መመሥከር’
    • መጽሐፍ ቅዱስና መጽሐፍ ቅዱሳዊ ጽሑፎች የያዙ ባልና ሚስት፣ ቤቱ ደጃፍ ላይ ለቆመ ሰው ሲሰብኩ።

      ሐዋርያት እንዳደረጉት ሁሉ እኛም “ከቤት ወደ ቤት” እየሄድን እንሰብካለን

      16. ሐዋርያቱ በሚገባ ለመመሥከር ቆርጠው እንደነበር ያሳዩት እንዴት ነው? እኛስ ሐዋርያቱ የተጠቀሙበትን የስብከት ዘዴ እየኮረጅን ያለነው እንዴት ነው?

      16 ሐዋርያቱ ወዲያውኑ ወደ ስብከቱ ሥራቸው ተመለሱ። ያለምንም ፍርሃት “በየቀኑ በቤተ መቅደስም ሆነ ከቤት ወደ ቤት እየሄዱ ስለ ክርስቶስ . . . የሚናገረውን ምሥራች . . . ማወጃቸውን ቀጠሉ።”d (ሥራ 5:42) እነዚህ ቀናተኛ ሰባኪዎች በሚገባ ለመመሥከር ቆርጠው ነበር። ኢየሱስ ክርስቶስ ባዘዛቸው መሠረት ከቤት ወደ ቤት እየሄዱ መልእክቱን ያውጁ እንደነበር ልብ በል። (ማቴ. 10:7, 11-14) በትምህርታቸው ኢየሩሳሌምን ሊሞሉ የቻሉት በዚህ መንገድ እንደነበር ምንም ጥርጥር የለውም። በዛሬው ጊዜም የይሖዋ ምሥክሮች የሚታወቁት ሐዋርያቱ በተጠቀሙበት በዚህ የስብከት ዘዴ ነው። ክልላችን ውስጥ እያንዳንዱን ቤት ማንኳኳታችን ምሥራቹን በሚገባ ለመመሥከር ያለንን ፍላጎት ያሳያል፤ ምክንያቱም ይህ የስብከት ዘዴ እያንዳንዱ ሰው ምሥራቹን የሚሰማበት አጋጣሚ እንዲያገኝ ያደርጋል። በእርግጥ ይሖዋ ከቤት ወደ ቤት በመሄድ የምናከናውነውን አገልግሎት ባርኮታል? አዎ፣ ባርኮታል! በዚህ በመጨረሻው ዘመን በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ሰዎች ለመንግሥቱ መልእክት ጥሩ ምላሽ እየሰጡ ነው፤ ከእነዚህ መካከል ደግሞ ብዙዎች ለመጀመሪያ ጊዜ ምሥራቹን የሰሙት የይሖዋ ምሥክሮች ቤታቸውን ባንኳኩበት ወቅት ነው።

      “ከቤት ወደ ቤት” መስበክ

      የሳንሄድሪን ሸንጎ በስብከት ሥራቸው ላይ እገዳ ቢጥልም ደቀ መዛሙርቱ “በየቀኑ በቤተ መቅደስም ሆነ ከቤት ወደ ቤት እየሄዱ” መስበካቸውንና ማስተማራቸውን ቀጥለው ነበር። (ሥራ 5:42) ለመሆኑ “ከቤት ወደ ቤት” የሚለው አገላለጽ ምን ያመለክታል?

      ካቲኮን የሚለው የግሪክኛ ሐረግ ቃል በቃል ሲተረጎም “በየቤቱ” ማለት ነው። በርካታ ተርጓሚዎች እንደገለጹት ከሆነ ካታ የሚለው ቃል ደቀ መዛሙርቱ ከአንድ ቤት ወደ ሌላው ቤት እየሄዱ ይሰብኩ እንደነበር ያመለክታል። ይህ ቃል በሉቃስ 8:1 ላይ በሚገኘው ዘገባ ላይም በተመሳሳይ መንገድ ተሠርቶበታል፤ ጥቅሱ እንደሚገልጸው ኢየሱስ “ከከተማ ወደ ከተማ እንዲሁም ከመንደር ወደ መንደር” እየተጓዘ ይሰብክ ነበር።

      ብዙ ቁጥርን የሚያመለክተው ካቲኩስ የሚለው ሐረግ ደግሞ በሐዋርያት ሥራ 20:20 ላይ ተሠርቶበታል። ሐዋርያው ጳውሎስ ክርስቲያን የበላይ ተመልካቾችን “በአደባባይና ከቤት ወደ ቤት ከማስተማር ወደኋላ ብዬ አላውቅም” ብሏቸው ነበር። አንዳንዶች እንደሚሉት ጳውሎስ እዚህ ላይ እየተናገረ ያለው በየሽማግሌዎቹ ቤት እየሄደ እንዳስተማረ አይደለም፤ በቀጣዩ ቁጥር ላይ ካለው ከሚከተለው ሐሳብ ይህን መረዳት ይቻላል፦ “አይሁዳውያንም ሆኑ ግሪካውያን ንስሐ እንዲገቡና ወደ አምላክ እንዲመለሱ እንዲሁም በጌታችን በኢየሱስ እንዲያምኑ በተሟላ ሁኔታ መሥክሬላቸዋለሁ” ብሏል። (ሥራ 20:21) የእምነት ባልንጀሮቹ ቀድሞውንም ቢሆን ንስሐ ገብተው በኢየሱስ አምነዋል። ስለዚህ ከቤት ወደ ቤት እየሄዱ መስበክና ማስተማር የሚለው ሐሳብ አማኝ ላልሆኑ ሰዎች መመሥከርን የሚያመለክት ነው።

  • “አምላክን እንደ ገዢያችን አድርገን ልንታዘዝ ይገባል”
    ‘ስለ አምላክ መንግሥት በሚገባ መመሥከር’
አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ